Fitih le Ethiopia

I wish democracy and unity for Ethiopia

Archive for the month “June, 2013”

በከፍተኛ ሙስና የተዘፈቀው መከላከያ ሂሳቡ እንዳይመረመር ታዘዘ

እንዳይመረመር ታዘዘ

 

-የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዚያ ወር 2005 ዓ.ም ባቀረበው ሪፖርት የመከላከያና የደህንነት ተቋማት
የፋይናንስ አያያዝ ከፍተኛ ችግር እንዳለበት ማመልከቱን ተከትሎ በየመ/ቤቶቹ የተነሳውን ቅሬታ ለመፍታት በቀጥታ
እነዚህን ተቋማት በተለየ ሁኔታ ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል አዋጅ እየተረቀቀ መሆኑ ተጠቆመ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ሚያዚያ 22 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማው ባቀረቡት የ2004 ዓ.ም
የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ ሪፖርት በተለይ በዘጠኝ መ/ቤቶች 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር
ባልተሟላ ሰነድ ወጪ ሆኖ መገኘቱን፤ ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ የመከላከያ ሚኒስቴር መሆኑን
መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
እነዚህ ተቋማት ላወጡት ገንዘብ ትክክለኛ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ተጠይቀውም ማቅረብ አለመቻላቸውን ለፓርላማው
ሪፖርት ካደረጉ በኋላ በተለይ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈረጌሳን ጨምሮ የተለያዩ ሹማምንት ሪፖርቱን
በአደባባይ እስከማብጠልጠል የደረሰ ትችት ሲያቀርቡ ተደምጠዋል፡፡ ዋናው መከራከሪያቸውም የመከላከያ ወጪ ሚስጢር
ነው የሚል ነበር፡፡

ይህንን ተከትሎ የፓርላማ አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ በቴሌቪዥን ቀርበው “ባልተሟላ ሰነድ
ወጪ ተደረገ ማለት ብሩ ተበላ ማለት አይደለም” በማለት ማብራሪያ ለመስጠትና ተቋሙን ከተጠያቂነት ነጻ ለማድረግ
ሞክረዋል፡፡

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያቸው የሆነውን መግለጫ ትላንት ጠዋት
በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡበት ወቅት በተመሳሳይ መንገድ መከላከያን ኦዲት ማድረግ
ሚስጢር ማባከን መሆኑን በመግለጽ በቀጣይ ሁኔታውን ለማስተካከል አዲስ ሕግ እንደሚወጣ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
ዋና ኦዲተር በአዋጅ ቁጥር 669/2002 መሰረት የፌዴራል የመንግስት ተቋማትን ኦዲት የማድረግና የማስደረግ ሙሉ ሥልጣን

እንደተሰጠው ጠቅላይ ሚኒሰትሩ አስታውሰው በዚህ ሕግ መሰረት ባለፉት ዓመታትም መከላከያን ጨምሮ ሁሉንም ተቋማት ኦዲት ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል፡፡

አቶ መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በሚያዚያ ወር 2004 ዓ.ም የ2003 የሂሳብ ሪፖርት ለፓርላማው ቀርቦ እንደነበር በዚህም ሪፖርት መሰረት

ከተወቀሱት ተቋማት መካከል መከላከያ አንዱ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ በ2003 በጀት ዓመት በመከላከያ 133 ነጥብ
8 ሚሊየን ብር ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩን፣ የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 19 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በወጪ
ተመዝግቦ መገኘቱን ሪፖርት አድርጓል፡፡  በተጨማሪም የወጪውን ትክክለኛነት ማረጋገጥ ካልተቻለው ገንዘብ መካከል 1
ነጥብ 9 ቢሊየን ብር የመከላከያ ሲሆን ፣ 54 ነጥብ 3 ሚሊየን ደግሞ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ 33
ነጥብ 34 ሚሊየን ብር የአገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ መሆኑ መጠቀሱ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መ/ቤቱ
እንደዘንድሮ ከፍተኛ ቅሬታ ያላቀረበ ሲሆን የዘንድሮ ቅሬታ ምናልባትም በአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ላይ ተጽዕኖ በማሳደር
ነገሩን ለመሸፋፈን የታሰበ ሳይሆን እንደማይቀር ተገምቷል፡፡

ምንጮቻችን እንደገለጹት በአገሪቱ ከፍተኛ ሙስና ከሚፈጸምባቸው ተቋማት መካከል ግንባር ቀደሙ መከላከያ መሆኑን
አስታውሰው አንድ ወርሃዊ ደመወዙ 4 ሺ ብር የማይሞላ ከፍተኛ የመከላከያ ሹም በአዲስአበባ ቁልፍ ቦታዎች ጭምር
በሚሊየን ብር የሚገመቱ ቪላዎችንና ሕንጻዎችን የሚገነባበት እንዲሁም ትልልቅ ንግዶችን የሚያንቀሳቅስበት ሁኔታ
የአደባባይ ሚስጢር ነው በማለት የእነአቶ ኃይለማርያም ሙግት ጥቅሙ ለሙሰኞቹ ነው ብለዋል፡፡
አዲሱ ሕግ በቀጣይ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ዋና ኦዲተር ሕጉ እስኪጸድቅ
መከላከያና የደህንነት ተቋማትን ኦዲት እንዳያደርግ መታዘዙንም ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ 60 ከፍተኛ ጀኔራሎች መካከል 58ቱ በትጥቅ ትግሉ ወቅት የህወሀት አባል ሆነው የመጡ ናቸው።

መከላከያን ከላይ ሆነው የሚዘወሩት 7ቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በሙሉ የህወሀት ታጋዮች ናቸው። ባለፉት 22 አመታት በዚህ ከፍተኛ

አመራር ውስጥ የሌላ ብሄር ተወላጅ ተካቶ አያውቅም።

በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ሀይለማርያም በአባይ ግድብ ዙሪያ ከተቃዋሚዎች ጋር እንደማይነጋገሩ አስታውቀዋል።

ኢሳት ዜና

ሰበር ዜና ፡ በጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላት መታሰራቸው ቁጣን ቀሰቀሰ

በጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላት መታሰራቸው ቁጣን ቀሰቀሰ -አንድነት በየትኛውም የመንግስት ህገወጥ ጫና ሰልፉን እንደማይሰርዝ ይፋ አድርጓል

HeadPic2

በጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 4 የአንድነት አባላት በፖሊስ መታሰራቸው በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ቁጣን ቀሰቀሰ፡፡ አንድነት ምንም አይነት ህገወጥ እስር በጎንደር የተዘጋጀውን የተቃውሞ ሰልፍ እንደማያስቆመው አሳውቋል፡፡

ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ በጎንደር  ሰኔ 30 የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ የሚመለከት በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩት አለልኝ አቧይ፣ ዋኘው፣አብርሀም ልጅ አለም፣አንጋው ተገኝ የተባሉት የአንድነት አባላት ህገወጥ በሆነ መንገድ በአካባቢው ፖሊሶች መታሰራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችን እንዳስቆጣ ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመላክቷል፡፡ ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ወረቀት በመበተናቸው ብቻ የታሰሩት ግለሰቦች ሁኔታ የስርአቱን አምባገነንነት አመላካች ነው፡፡

የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች “እስር ለጎንደር ነዋሪ በተለይም ለአንድነት አባላት አዲስ አይደለም” ካሉ በኋላ “የታሰሩት አባሎቻችንን ለማስፈታት ከምናደርገው ጥረት ጎን ለጎን የቅስቀሳ ስራው እንዳይስተጓጎል ተጨማሪ አባላት የቅስቀሳ ስራውን እንዲቀጥሉ ወደ ስፍራው ልከናል፡፡” ብለዋል፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሙላት ጣሰው ለሰሜን ጎንደር አስተዳዳሪ ለአቶ ግዛቴ አብዩ ስልክ በመደወል የታሰሩት የአንድነት አባላት በአፋጣኝ መፈታት እንዳለባቸው ተናግረው ገዢው ፓርቲ የሚያደርገው አፈና ከህዝባዊ ንቅናቄ እንቅስቃሴያችን አያስቆመንም በማለት አሳስበዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ የሚጠበቅበትን ስለሰልፉ የማሳወቅ ተግባር አጠናቆ ቅስቀሳ የጀመረ ቢሆንም በበጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ የተቃውሞ ሰልፉን አላማ የሚያብራራ በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩ አባላቱ በህገወጥ መንገድ ከመታሰራቸውም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች የአንድነት ፓርቲ የቅስቀሳ ቡድን አባላት የሚደርስባቸውን ማስፈራሪያ ወደ ጎን ብለው ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸውንና የአከባቢው ነዋሪም በራሱ ተነሳሽነት በራሪ ወረቀቶችንና መረጃዎችን በማስተላለፍ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ጎንደር ዞን አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታውቀዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ በጎንደር ለሚደረገው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ የጎንደር ከተማና አከባቢው ነዋሪዎች በስፋት እንዲሳተፉ በቀየሰው ስትራቴጂ መሰረት ስኬታማ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ሁለተኛው የቅስቀሳ ቡድንም ዛሬ ወደ ጎንገር መንቀሳቀሱ ታውቋል፡፡

ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት

http://www.clickhabesh.com

posted by Tseday Getachew

በድጋሚ የወጣ የአቋም መግለጫ፤ ድምጼን ከፍ አድርጌ እደግመዋለሁ!

kubbaa10

እኔ ኦሮሞ ነኝ፡፡ ኦሮሞነቴን የሰጡኝ አባቴእና እናቴ ናቸው እንጂ ከሱፐር ማርኬት ገዝቼው አይደለም፡፡ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ኢትዮጵያዊነቴን ያገኘሁት ከእናትእና ከአባቴ እንጂ አንዳች አካል እላዬ ላይ ለጥፎብኝ አይደለም፡፡ በኢትዮጵያዊነቴ እንደምኮራው ሁሉ ኦሮሞነቴም ኩራቴ ነው፡፡

በኢትዮጵያ በርካታ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተዟዙሪያለሁ፡፡ የዛን ጊዜ ከ”አካም ቡልተኒ” ውጪ ምንም ኦሮምኛ አላውቅም ነበር፡፡ ነገር ግን በየባላገሩ ያሉ ኦሮሞዎች የኔ አማርኛ ተናጋሪ መሆን፤ ወይም ኦሮምኛ ቋንቋ አለመቻል አንድም ቀን አሳስቧቸው አያውቅም፡፡ ሰው በመሆኔ ብቻ አክብረው እርጎ አቅርበውልኝ፣ እርጎ የሆነ ፈገግታ ለግሰውኝ፣ ለራቸው ከሚተኙበት የተሸለ መኝታ ሰጥውኝ በእንክብካቤ ነው የሚያስተናገዱኝ፡፡

አንዳንዶች፤ ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ አልመሆኑን ሊነገሩኝ ታሪክ እንዳነብ፣ አዋቂ እንድይቅ፣ ጸሎት እንዳደርግ ሁላ መክረውኛል፡፡ እኔ ግን ይሄንን ሁሉ ማድረግ ሳያስፈልገኝ ከኦሮሞ የሚፎካከር ኢትዮጵያዊ እንደሌለ አሁን በቅርቡ የዞርኩባቸው የኦሮሚያ ገበሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡ ይህንን ነገር እኔ ብቻ ሳልሆን በቅርብ የኦሮሞን ህዝብ ጠንቅቀው የሚያውቁት እነ ጀነራል ከማል ገልቹ አረጋግጠውታል፡፡ እነ አቶ ቡልቻ ደመቅሳም መርቀውታል፡፡ ለዛም ነው ዛሬ የጀነራል ከማል ገልቹ ኦነግ በስፋት ተቀባይነት እያገኝ የመጣው፡፡ ለዛም ነው ዛሬ የኦሮሞ ልጆች በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያሸበረቀ የኦነግ አርማን  ከአረንጓዴ ቢጫ ቀዩ የሀገራቸው ባንዲራ ጋር ጎን ለጎን ይዘው በአደባባይ ስለ ኢትዮጵያ ልጆች የሚጮሁት!

ለብቻ መኖር የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ቢሆን ኖሮ እንደ ኦሮሞ ህዝብ ጀግንነትእና ብዛት፤ ጮክ ብዬ እደግመዋለሁ እንደ ኦሮሞ ህዝብ ጀግነነትእና ብዛት፤  አርባ አመት ፈጅቶ አይኮላሽም ነበር፡፡

በአሁኑ ጊዜ የኦሮሞ ህዝብ እየተበደለ እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡ በርካታ ወዳጆቼ ኦሮምኛ ተናጋሪ ስለሆኑ ብቻ ኦነግ ናችሁ ተብለው ከዩንቨርስቲ ወጥተው እስር ቤት ገብተዋል፡፡ ከስራቸው ተባረው ለስደት ተዳርገዋል፡፡ ወዘተ ተደርገው ወዘተ ሆነዋል፡፡ ልክ እንደዛ ሁሉ ግን በደሉ ሌሎችም ዘንድ አለ፡፡ አማራውም ትግሬውም አዲሳቤውም ሁሉም ቁስል አለበት፡፡

አብሮ ታክሞ አብሮ መኖር ለሁሉም ይበጃል!!!

http://www.abetokichaw.com/

posted by Tseday Getachew

ወይዘሮ አዜብ እና ”ለመንግስት ተመላሽ ሊደረግ የነበረ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000)

 

qw

ስብሃት ነጋ …ህዝብን የሚያደነቁሩትን እነበረከትንና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያምን እርቃናቸውን አስቀሩ::
ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ።
አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..
ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ « አላማና ግብ » አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ « .በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ። » ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..«አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች።
« ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።
ስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ።
አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

posted by Tseday Getachew

የአብዬን ወደ እምዬ

Jወያኔና ከወያኔ አፍ የሰሙትን ሁሉ እንደበቀቀን እየደጋገሙ የሚያነበንቡ ሎሌዎች የራሳቸውን መልክ የሚያዩበት መስታወት የተቸገሩ ይመስላል። ወየኔና ሎሌዎቹ እራሳቸውን ማየት ስለተሳናቸው ህዝብም ልክ እንደ እነሱ ኣራሱን የማያይና እነሱንና እኩይ ስራቸዉን የማያዉቅ እየመሰላቸው ሄዷል፡፡ ለዚህም ነዉ በግፈኛ አገዛዛቸው ተንገፍግፎ የሚቃወማቸውን ሁሉ ጥላሸት ለመቀባትና በራሳቸው ስም ለመጥራት ሲንጠራሩ የሚታዩት።

የወያኔ ዘረኞች የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ኃይሎች በሙሉ በፀረ-ኢትዮጵያዊነትና የአገርን ጥቅም ለባዕድ አሳልፎ በመሸጥ ሲከስሱ ስንሰማ አይናቸዉንና ፊታቸዉን ታጥበዉ አይነ ደረቅ ለመመሰል ስንት ኪሎ ጨው እንደፈጀባቸዉ መገመት ያዳግታል።

በአገራችን ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በኢትዮጵያ ህልውናና በወሳኝና ዘላቂ ጥቅሞቿ ላይ የዘመተ ኃይል ኖሮም ተፈጥሮም አያውቅም። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጀግኖች አባቶቻችን አጽም ያረፈበትን መሬት በስጦታ ለጎረቤት አገር እናካችሁ ብሎ የሰጠ ማነዉ? ማነው በሽፍትነት ዘመኑ ለተደረገለት ውለታና ተቀናቃኞቹን እንዲጠብቁለት በማሰብ የኢትዮጵያን ድንበር እንደ ዳቦ እየገመሰ ለባዕዳን የሸጠው?

ማነው የገዛ ወገኑን ከአያት ቅድመ አያት አጽመ ርስቱ ላይ እያፈናቀለ አንድ ሲኒ ቡና በማይገዛ ገንዛብ ለምለም መሬታችንን ለባእዳን የሚያቀራምተው? ማነው በህዝብ ስም በልመናና በችሮታ የተገኘን ገንዘብ እየዘረፈ ከአገርና ከህዝብ ደብቆ የባእድ አገር ባንኮችን የሚያደልበው? ኢትዮጵያ በሶማሊያ በተወረረችበት በ1970ዎቹ አመታት የሞቃዲሾን ፓስፖርት ተሸክመው ይንጎማለሉ የነበሩት የዛሬዎቹ የወያኔ አለቆች መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ ገና አልረሳዉምኮ!

የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ትናንት የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት ማየት ከማይፈልጉ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጋር እጅና ጓንት ሆነዉ የኛን የጎሳ ድርጅት እስከረዳችሁ ድረስ ኢትዮጵያን እናደክምላችኋለን የሚሉ ጸረ አገርና ጸረ ህዝቦች ነበሩ።እነዚህ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ዛሬ አይናቸዉን በጨው አጥበዉ እራሳቸዉን የኢትዮጵያ ጥቅም አስከባሪ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነትና ለአገር አንድነት መከበር የሚታገሉትን ዉድ የኢትዮጵያ ልጆች የአገር ጠላት ብሎ ለመጥራት የሚያበቃ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያክል የሞራል ብቃት የላቸውም።

ወያኔዎች ስልጣን በያዙ ማግስት በጻፉትና እነሱን ሲጠቅም በሚጠቅሱት አገርንና ህዝብን ሲጠቅም ግን እየዳጡ በሚያልፉት ህገመንግስት ዉስጥ ደደቢት በረሃ የወሰዳቸዉን ዋነኛ አላማ መገነጣጠልን እንደ አገር ጥቅም በጹሁፍ ካልሰፈረ ብለው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩበትን ጊዜ እኛ የኢትዮጵያ ነገር የሚቆረቁረን ወገኖች አልረሳነውም። ለመሆኑ ሌሎችን በጸረ-ኢትዮጵያዊነት የሚከሰው ወያኔ እውነት ኢትዮጵያን ከወደደ መገነጣጠልን ለምን ተመኘላት? መገነጣጠልን የመሰለ አደጋ እንደ ብሔራዊ የአገር ጥቅም አይቶ የራሱን ምኞት በህግመንግስት ደረጃ ያጸደቀዉ ወያኔ እንዴት ሆኖ ነው ለኢትዮጵያ አንድነትና ክብር የሚጋደሉና የሚታገሉ ልጆቿን በሀገር ጠላትነት የሚከስሰው? የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ ጋር የሚደረገዉን ትግል ከመብትና ከነጻነት ትግል ባሻገር እንደ አገር አድን ትግል አድርጎ የሚመለከተዉ ይህንኑ ወያኔ በአገራችን ብሄራዊ ጥቅሞች ላይ በተደጋጋሚ ያሳየዉን ጠላትነት በመገንዘብ ነዉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ተቃዋሚ ኃይሎችን በጅምላ የአገር ጠላት ለማስመሰል በሚቆጣጠራቸዉ የመገናኛ አዉታሮችና በታማኝ ሎሌዎቹ በኩል የጀመረዉን የስም ማጥፋት ዘመቻ ከወዲሁ ተረድቶ “የአብዬን ወደ እምዬ” ብሎ ትግሉን ከቀጠለ ዉሎ አድሯል። ወያኔና ለሆዳቸው ያደሩ ሎሌዎች ሁለመናቸውን የወረሰውን የፀረ-ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊነት እከክ ማንም ላይ ማራገፍ አይችሉም። ድፍን ኢትዮጵያ ማንነታቸውን አሳምሮ ያውቃልና።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

posted by Tseday Getachew

ኦባማ – “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

“ግብረሰዶማዊነት ወደፊት!”

obama in senegal

J
በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍሪካን እየጎበኙ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሴኔጋል ጉብኝት ባደረጉት ወቅት የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር እንደሚገባው አስታወቁ፡፡ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት ሰዶማውያንን የሚደግፍ ውሳኔ ሰሞኑን በማሳለፉ ደስታቸውን ገለጹ፡፡ የሴኔጋሉ አቻቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይወነጀሉ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናገሩ፡፡

ሰሞኑን በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝታቸውን በጀመሩባት ሴኔጋል የግብረሰዶማውያንን መብት በተመለከተ ለአፍሪካውያንና ለመሪዎቻቸው ማብራሪያና “ትምህርት” ሰጥተዋል፡፡ “መንግሥታት ዜጎቻቸውን እንዴት ሊያስተናገዷቸው ይገባል፤ ሕጉስ እንዴት ሊያያቸው ይገባል ለሚለው ጥያቄ መልሱ ሁሉም ሰው በእኩልነት ሊስተናገድ ይገባዋል” በማለት “ግብረሰዶማዊነት ወደፊት” የሚያስብል ንግግር አድርገዋል፡፡

አፍሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ኦባማ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት የግብረሰዶማውያንን መብት ሊያስከብር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፉ እንዳስደሰታቸው በጉብኝታቸው ወቅት ጠቁመዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ያስተላለፈው ውሳኔ ለጋብቻ መጠበቅ ከለላ የሚያደርገውን Defense of Marriage Act (DOMA) የተባለው ሕግ ለወንድና ሴት ተጋቢዎች ብቻ በማለት ያስቀመጠው ከለላ የግብረሰዶማውያንን መብት ይጻረራል በማለት ነበር፡፡ ስለሆነም በፍርድቤቱ ውሳኔ መሠረት  በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል የተፈጸመ “ጋብቻ” ከፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞችን ሊያስከለክል አይገባም በማለት ወንድ ሚስትም ሆነ ሴት ባል ያላቸው ሁሉ የጥቅሙ ተካፋይ እንዲሆኑ ፈቅዶላቸዋል፡፡ እንዲሁም በካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት የሰዶማውያን ጋብቻ እንዲቀጥል ፈቃድ የሚሰጥ ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድቤቱ አስተላልፏል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በበርካታ የአፍሪካ አገራት ግብረሰዶማዊነት በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በበኩላቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይከሰሱ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናግረዋል፡፡ “በጣም በመቻቻል” የምንኖር ነን ያሉት የሴኔጋሉ መሪ አገራት ውስብስብ የሆኑ ሕጎችን በራሳቸው ጊዜ በተግባር ላይ እንደሚያውሉ በመጥቀስ የኦባማን ሃሳብ ተግሳጽ በተሞላበት ምላሽ አስተናግደውታል፡፡

በመቀጠልም አገራቸው ሴኔጋል ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት ያቆመች መሆኗን በመናገር አሜሪካ ግን ይህንን እስካሁን ተግባራዊ አለማድረጓን በመጥቀስ ኦባማን ተሳልቀውባቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአሜሪካ ወንጀለኞችን በሞት የመቅጣት ህግ ከ30 በላይ ግዛቶች ውስጥ ተግባራዊ ሲሆን በተለይም በቴክሳስ በሰፊው እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት እንደገና ከተጀመረ ከ1974ዓም በኋላ የቴክሳስ ጠቅላይግዛት 500ኛዋን ወንጀለኛ ሰሞኑን በመግደል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዞ ይገኛል፡፡

“ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

በፈረንሣይ አብዮት አካባቢ ህዝቡ መራቡን በተለይም የፈረንሣይ ጭሰኞች መቸገራቸውና በረሃብ እየተንገላቱ መሆናቸውን የተነገራት ልዕልት ማሪ አንቷኔ (“Qu’ils mangent de la brioche”) “ከራባቸው ኬክ ይብሉ” ብላ መልሳለች እየተባለ ለዘመናት ሲዘበትባት ኖሯል፡፡ ልዕልቲቱ ይህንን ለማለትዋ የተረጋገጠ ነገር ባይሆንም ነጻነት፣ መልካም አስተዳደር፣ ዴሞክራሲ፣ ፍትሕ፣ … ለጠማው የአፍሪካ ሕዝብ ባራክ ኦባማ “የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር ይገባል” በማለት መሠረታዊውን የህዝብ ጥያቄ ችላ ማለታቸው “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” የማለት ያህል እንደሆነ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡

በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት “ለውጥ” እና “ተስፋ” ቀዳሚ ዓላማቸው አድርገው የበርካታዎችን ቀልብ የሳቡት ባራክ ኦባማ፤ ለአፍሪካ መሠረታዊ ችግር እስካሁን ጆሮ አለመስጠታቸው ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ሰሞኑን በአሜሪካ ምክርቤት “ኢትዮጵያ፤ ድኅረ መለስ” በሚል ርዕስ በተደረገው ምክክር የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የተናገሩትን በድጋሚ ያስታወሱም አሉ፡፡ በወቅቱ አቶ ኦባንግ ያሉት “ኦባማ ለምርጫ በተወዳደረ ጊዜ ጥቂት ደመወዝ የሚከፈላቸው ኢትዮጵያውያን የምርጫ ዘመቻውን ደግፈው ነበር፤ እስካሁን ከኦባማ የሰሙት ነገር የለም” በማለት ነበር፡፡

ከምዕራባውያን የሚመነጨውን ማንኛውንም ነገር – ከፖለቲካ እስከ ማኅበራዊ አመለካከት – ትክክለኛ አድርገው ለሚቀበሉ ግብረሰዶማዊነት ሥልጣኔ ይመስላቸዋል በማለት ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ የሃይማኖትና የማኅበረሰብ ሳይንስ ጉዳዮች ምሁር “ጋብቻ” የሚለውን ቃል ለሁለት ወንዶች መጠቀም እርስበራሱ የሚጋጭ ጉዳይ ነው በማለት ተመሳሳይ ጾታ ብሎ ጋብቻ ማለት የተሳከረ አነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ “ይህ የሰዶማውያን መብት ይከበር የሚለው ጉዳይ በሕግ እየጸደቀ ሲሄድ ድርጊቱን ከሃይማኖታቸው አኳያ የሚቃወሙ ሰባኪያን የሃይማኖት ትምህርታቸውን በሚያስተምሩበት ቤ/ክ ይሁን መስጊድ ወይም ምኩራብ ግብረሰዶማዊነትን እየተቃወሙ ሰበካ ማድረግ በህግ የሚያስጠይቃቸው ይሆናል” በማለት ወደፊት ሊመጣ የሚችለውን የማኅበረሰብ ቀውስ ጠቁመዋል፡፡

bush in africaበሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው ወቅት ዳግም የመመረጥ ፈተና የሌለባቸው የአሜሪካ መሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን የአፍሪካን የዱር እንስሳት እየጎበኙ ወደፊት ለሚሠሩት ፕሬዚዳንታዊ ቤተመጻህፍት (ፋውንዴሽን) ፎቶ እንደሚሰበስቡ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ የባራክ ኦባማም ጉብኝት ከዚህ የተለየ አለመሆኑ ግልጽ ሲሆን “የአፍሪካ ልጅ” እየተባሉ ሲሞካሹ የኖሩት ፕሬዚዳንት ዛሬ ደቡብ አፍሪካ ሲገቡ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ ገጥሟቸዋል፡፡ ቅዳሜ የክብር ዶክትሬት በሚቀበሉበት የዮሐንስበርግ ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ ተቃውሞ ይጠብቃቸዋል፡፡

ዛሬ ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ደቡብ አፍሪካውያን “ይቻላል” (Yes! We can!) ለሚለው የኦባማ የምርጫ መፈክር “አትችልም!” (“No, You Can’t Obama,”) የሚሉ መፈክሮችን በመያዝ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ “ኦባማ የመጣው አፍሪካንና ደቡብ አፍሪካን ለመዝረፍ ነው” በማለት ጠንካራ ተቃውሞውን የገለጸው አንዱ ተሰላፊ “አፍሪካውያን በብዙ መልኩ እየተሰቃዩ እያለ እርሱ ግን የአፍሪካን ሐብት፤ ወርቅ፣ አልማዝ፣ … ለመዝረፍ ነው የመጣው” ብሏል፡፡obama s africa

የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕ፣ … ዕጦት ላንገላታውና በአምባገነኖች መዳፍ ሥር ለሚሰቃየው የአፍሪካ ሕዝብ በቃላት እንኳን ድጋፋቸውን ከመስጠት እስካሁን የተቆጠቡት ኦባማ አሜሪካ በአፍሪካም ሆነ በሌሎች አገሮች ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ፍላጎቱ እንደሌላት በማያወላውል መልኩ ያረጋገጠ መሆኑ የብዙዎች ግንዛቤ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፕሬዚዳንቱን የሥልጣን ኃይል ጥያቄ ውስጥ የሚጥልም ነው፡፡

በአውሮጳ የፖለቲካ ምጣኔሃብት ተመራማሪ የሆኑ እንደሚሉት “አሜሪካኖች እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ ዓይነቱን አምባገነናዊ አገዛዝ እስኪያስመልሰው ድረስ በዕርዳታ ገንዘብ ካሽሞነሞኑ በኋላ “ኢህአዴግን ምን እናድርገው” በማለት “ምክር ስጡን” እያሉ በሕዝብ ሰቆቃ ላይ ያላግጣሉ፡፡ ሲሻቸውም ደግሞ አፍሪካ ድረስ በመሄድ “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” በማለት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን ችግር ያልሆነውን የግብረሰዶማውያን መብት መከበር ይሰብኩናል፡፡ ታዲያ ለዚህ ልግጫ መልሳችን መሆን የሚገባው “ራሳችንን ነጻ እናወጣለን፤ ነጻነታችንን አንለምንም፤ አሜሪካ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት እንድትሆንብን አንፈልግም” በማለት አቶ ኦባንግ ሜቶ ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ምክርቤት በተካሄደው ምክክር የተናገሩትን ዓይነት ቁርጠኝነት ነው በማለት አስተያየታቸውን ደምድመዋል፡፡

obama africa trip100ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣው የኦባማ የአፍሪካ ጉብኝት በአሁኑ ጊዜ በበጀት ቀውስ ምክንያት በርካታ ሠራተኞች ደመወዛቸው እየተቆረጠ ባለባት አሜሪካ አነጋጋሪ መሆኑን ዋሺንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡ የደኅንነት ሰዎችን እንዲሁም 14ሊሞዚን፣ 56 ጥይት የማይበሳቸው ድጋፍ ሰጪ  መኪናዎች፣ ሙሉ የህክምና ባለሙያዎችን የያዘና ጀቶችን የጫነ መርከብ … ለፕሬዚዳንቱና ለቤተሰባቸው ጥበቃ በማድረግ ሥራ ላይ እንደሚውሉ ጋዜጣው ያብራራል፡፡

ፕሬዚዳንት ኦባማ በደቡብ አፍሪካ የሁለት ቀን ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሰኞ ወደ ታንዛኒያ ያመራሉ፡፡ የአባታቸው የትውልድ አገር ነው የሚባለውን ኬኒያ ሳይረግጡ በዚያው ወደ አገራቸው እንደሚያቀኑ የጉዞ መርሃግብራቸው ያስረዳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

posted by Tseday Getachew

ጃዋር መሃመድ እና የአማራ ሊሂቃን

ጃዋር-መሃመድ

ከያሬድ አይቼህ – ጁን 28፥2013

የኦሮሞ-አማራ ምሰሶነት ንድፈ-ሃሳብ በቀረበበት በዚህ ሰሞን ፡ አቶ ጃዋር መሃመድ በአልጀዚራ ቲሌቪዥን ላይ “መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ … ኢትዮጵያዊነት ያለፈቃዳችን ተጭኖብን ነው” ማለቱ ለሁለቱ መሰሶዎች ሊሂቃን አብሮ መስራት ፍላጎት የመጀመሪያው የአደባባይ ፈተና ሆኗል። ሁለቱ ምሰሶዎች አብረው መስራት የሚችሉት ለሁሉም ብሄሮች የሚበቃ ምህዳር ያለው ‘ኢትዮጵያዊነት’ ሲቃኝ ብቻ ነው። ሌላ አቋራጭ መንገድ የለውም።

– ኢትዮጵያዊነት እና አማራነት –

አማራዎች አንድ መሰረታዊ ችግር አለብን። እኛ አማራዎች ኢትዮጵያዊነትን እና አማራነትን ለይተን ማየት ተስኖናል። በተለይ አሮጌው ትውልድ በፍጹም ኢትዮጵያዊነትን ከአማራነት ፡ አማራነትን ከኢትዮጵያዊነት ለያይቶ ማየት የማይችል የአስተሳሰብ መካኖችን በብዛት አሉበት።

እኛ አማራዎች ‘አንድነት’ ስንል ‘አንድ አይነትነት’ ማለታችን መሆኑ ተነቅቶብናል። አሃዳዊት ኢትዮጵያ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ያልጠቀመች ኢትዮጵያ ነበረች። አሁን ብዙአዊት ኢትዮጵያ ነግሳለች። ብዙአዊት ኢትዮጵያ የጃዋር መሃመድ ኢትዮጵያ ናት። ብዙአዊት ኢትዮጵያ የሌንጮ ባቲ ኢትዮጵያ ናት። ብዙአዊት ኢትዮጵያ የዋለልኝ መኮንን ኢትዮጵያ ናት።

አማራዎች ሆይ! የዱሮዋ ኢትዮጵያ ተመልሳ አትመጣም። አማርኛ ቋንቋ ሁሉም የሚናገርባት ፡ ኦርቶዶክስ ክርስትና የተንሰራፋባት ፡ አርንጓዴ-ቢጫ-ቀይ ብቻ የሚውለወለብባት ያች ኢትዮጵያ በታሪክ መጽሃፍት እና በቪዲዮ እንጂ ወደፊት ልትመለስ አትችልም። የአሃዳዊ ስርዓት ናፋቂዎች እርማችንን እናውጣ!

– አዲስ ኢትዮጵያዊነት –

ባለፉት 22 አመታት ኢትዮጵያዊነት እንደገና ተቀርጿል ፤ አዲስ መልክ ተላብሷል። ኢትዮጵያዊነት የአማራዎች ሶፋ መሆኑ ቀርቶ ለሁሉም የሚበቃ ሰፊ አግዳሚ ወንበር ሆኗል። “መጀመሪያ ብሄሬን ነኝ ፡ ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ ነኝ” የሚለው አስተሳሰብ በትግሬዎች ሲነገር ሃሰት ቢሆንም ፤ በምስራቅ ፡ ምዕራብና ደቡብ ኢትዮጵያዊያን ቢነገር ግን ሃቅ ነው።

ትግራያን የሚዘነጉት እውነታ ቢሆር አማርኛን ቋንቋ የኢትዮጵያ መንግስት ቋንቋ ያደረጉት አጼ ዮሃንስ መሆናቸውን ነው። ይሄን እውነታ እያወቁ የትግራይ ሊሂቃን ክህደት ውስጥ የገቡት ህወሃት በኦሮሞዎች እና በአማራዎች ላይ የፓለቲካ የበላይነት ለመያዝ ብሎ ነው።

በአዲሱ ኢትዮጵያዊነት ፡ ኢትዮጵያውያን ብዙ አይነት ማንነት አላቸው። ዜጎች አንድ አይነትነትን እንደ ኢትዮጵያዊነት አይቀበሉም። አቶ ጃዋር እንደገለጸው ፡ አንድ አይነትነት በግዴታ የሚጫን ማንነት ነው። በሰፊው ኢትዮጵያዊነት ግን ብዙ አይነትነትን የሚያስተናግዱ ፡ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረቱ ማንነቶች ተንሰራፍተዋል።

– የጃዋር ቁንጥጫ –

ጃዋር የቀድሞው ስርዓት ናፋቂዎችን ትዝታና የፓለቲካ ቱሪስትነት በንግግሩ ቆንጥጦታል። የትዝታ ፓለቲካ ለምንወድ የጃዋር ንግግር ያበሳጫል ፤ ንግግሩ ግን ታሪካዊ ጭብጥ ነው። የአገራችን የፓለቲካ ውጥረት በትዝታና በፓለቲካ ቱሪስትነት የሚፈታ አይደለም።

ለሁለቱ ምሰሶዎች አብሮ መስራት የአማራ ሊሂቃን የጃዋር መሃመድን ንግግር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበላቸው የመጀመሪያ ፈተና ነው። ይሄን ማድረግ ያቃታችሁ የአማራ ሊሂቃን ፡ በተለይ በቀድሞው የአሃዳዊ ስርዓቶች ነፍስ ያወቅን ፡ ከትግሉ ጡረታ ውጡ። እናንተ ለሁለቱ ምሰሶዎች አብሮ መስራት ዋና እንቅፋትና ፡ መርዝ ናችሁና ገለል በሉ። መርዛችሁ ለኢትዮጵያዊነት መስፋፋት ፡ መዳበር እና እመርታ እንቅፋት ነውና ዞር በሉ:: አዎ! ዞር በሉ!!

ክብር ለጃዋር መሃመድ!

ቪቫ ኦሮሚያ! ቪቫ ኢትዮጵያ
የጸሃፊው አድራሻ፦ yared_to_the_point@yahoo.com

Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=4806

posted by Tseday Getachew

ስብሃት ነጋ “እውነት” ሲያዳልጣቸው

Jከኢየሩሳሌም አርአያ

ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ “አላማና ግብ” አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ “በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ።” ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..« አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች። በተለይ ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ። በማስከተልም ፥ « ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው <ሉሲ አካዳሚ > በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።sebehat nega one of the founders of TPLF

ስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ። አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..

አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

http://ecadforum.com

posted by Tseday Getachew

 

በአዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጥያቄዎችህ እየቀረቡ ነው::

by ጃፋር

Ethiopia: Azeb Mesfin, EFFORT Employees Vow to Make the Late PM Meles Zenawi’s Vision a Reality
እነመላኩ ፋንታን ተከትሎ በአዜብ መስፍን ላይ የሚቀርቡ የሙስና አቤቱታዎች ጨምረዋል::
የሙስና ኮሚሽን በአቶ ገብረዋህድ ቤት ባደረገው ፍተሻ እንዲሁም ከኣሁን ቀደም በመርማሪ
ደህንነቶች ክትትል በተደረገ የስልክ ጠለፋ የቀድሞ ሟች ጠ/ሚ ባለቤት እና በአለም ትልቁ
የሙስና አባት ኤፈርት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገብረዋህድ ባለቤት እና
እህት ጋር በከፍተኛ ደረጃ የቢዝነስ ስራ ይሰሩ እንደነበር እና ከታሰሩት ባለስልጣናት እና
ባለሃብቶች ጋር የንግድ አጋርነት እንዳላት አረጋግጧል::ይህንን የሚጠቁሙ ሰነዶች እና
ከተለያዩ ወገኖች የሚቀርቡ ጥቆማዎች እና አቤቱታዎች ምርመራው ወደ አዜብ መስፍን
አምርቶ ለጥያቄ እንደምትፈለግ ፍንጭ እየሰጠ ነው ሲሉ የሙስና ኮሚጽሽን የውስጥ አዋቂ
ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::ለሙስና ኮሚሽን ከደረሱት አቤቱታዎች ከፊሎ
ቹ :-ኤፈርትን ተገን በማድረግ የተለያዩእቃዎችን ካለቀረጥ እያስገባች ነው:: ኤፈርት ለመንግስት መክፈል የሚገባውን ህጋዊ የግብርም ሆነ ሌላ ክፍያዎች እንዳይፈጸም አድርጋለች::

ዩዲ ኒሳን ዲዝል ገልባጭ መኪኖችን ካለቀረጥ ነጻ በማስገባት በአቶ ከተማ ከበደ/ኬኬ/ ስም ሸጣለች::

ከዚህ ቀደም እያሱ በርሄ ጋር በኋላም ከኮሎኔል ሃይማኖት ጋር የተከለከሩ የቴለኮሚኒኬሽን ኬብሎችን

እና ቴክኖሎጊካል የመገናኛ መሳሪያዎችን ካለቀረጥ በማስገባት ሰርታለች::በነጻ ትሬዲንግ በኩል የተለያዩ

ዘመናዊ መኪኖችን ካለቀረጥ እያስገባች በአቶ ነጋ ገ/ዝጌር ስም ትሸጣለች::በሰበታ አለምገና አከባቢ

የአበባ ሰፊ እርሻዎች አላት :: በህገወጥ የዶላር እና የኢሮ ዝውውር ውስጥ መሪ ተሳታፊ ናት::

ባንክ ኦፍ ማሌዥያ እና የሲንጋፖር ባልሃብቶችን እንዲሁን ቻይናውያንን በህገወጥ አለማቀፍ

የገንዘብ ዝውውር ተባባሪ አድርጋ እየሰራች ነው::በተለያዩ አረብ አገራት እና በሃገር ውስጥ

ባስቀመጠቻቸው ደላሎች ኢትዮጵያውያን ሴቶችን በሱዳን እና በየመን አድርጋ ወደ አረብ አገራት ትሸጣለች:

:በተለያዩ የቤተሰብዋ አባላት ስም ባወጣችው የኮንስትራክሽን ንግድ ፍቃዶች ጨረታዎችን በጉልበት ከመቀማት

እየሰራሽ ሲሆን ሌሎች ባለሃብቶችን በስማቸው በመጠቀም የተለያየ ቢዝነሶችን እያካሄደች ነው የሚሉ አቤቱታዎች

እና ጥቆማዎች ለሙስና ኮሚሽን የመርማሪዎች ቡድን ደርሷል::

ይህንን ተከትሎ ጠንካራዎቹ የወያኔ አባላት በወይዘሮ አዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ

ግፊት እያደረጉ ሲሆን ወይዘሮዋ በአሁን ሰአት ራሳቸውን በተለያየ ምክንያት ገኖ ለማውጣት

ላይ ታች እያሉ መሆኑን ታውቋል::

 
 
posted by Tseday Getachew
 

ዓባይና የመለስ ዜናዊ (ወያኔ) ታላቁ ሴራ!

 

ሰሞኑን የአለምንና የኢትጵያውያንን ሀሳብና አስተየት ለመለዎጥ ወይም ለማሳሳት ወያኔ በወኪሎቹ አማካይነት የተለመደዉን ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ከርሞአል። ዓባይ እንደሚጠቅመን ሆኖ ቢገደብልን እጂግ ደስ ይለን ነበር። የወያኔ ትግሬዎች ሰለአባይ ከባለቤቱ ከኢትጵይያ ህዝብ በላይ የሚያቀነቅኑበት የሚጮሁበትና ሚያስመስሉበት ምክንያቱ ሌላ ነው። እነሱ ሃገር ወዳድ ሌሎች ኢትዮጵዉያን ሀገራቸዉ ብታድግና ብትጠቀም የሚጠሉ ሆነው አይደለም።

የኢትዮጵያም ህዝብ ይህንን በደንብ ያዉቀዋል። ከእባብ እንቁላል እርግብ ኣልጠብቅም ብሎአቸዋ። ታዲያ ይኸ ሁሉ የአዞ እንባ ማፍሰስና የኢትዮጵያን ሀዝብ ጩኸት ለመቀማት የመሞከር ሚስጥሩ ምንድነው??? ወያኔ ኢትዮጵያን ለመጉዳትና ለረጂም ጊዜ እችግር ዉስጥ ለማስገባት ካስጠናቸዉ ትልልቅ ጉዳዮች (ፕሮጀችቶች) ኣንደኛዉና ዋናው የአባይ ግድብ ነው። ለዚህም ማስረጃ የሚከተሉትን ነጥቦች ተመልከቱ:

ሀ) ግድቡ የሚሰራው በጥንቃቄ የመሀል ሀግሩን ህዝብ በተለይም አማራዉንና ኦሮሞዉን እንዳይጠቅም በጣም እርቆ በጠረፍ ላይ ነዉ። ይህም በተለይ አማራዉና ሌሎች በአካባቢው የሚኖሩ ህዝቦች በምንም አይነት ለእርሻ (ለመስኖ) ለመጠጥ ለኢንዱስትሪና ለኤሌክትሪክ ኣገልግሎት እንዳይጠቀሙ ታስቦ የተሰራ ነው።

ለ) ሁለተኛዉ የተንኮል አካል ይኽ ጥቅም የማይሰጥ ነገር ግን ሆን ተብሎ በኣካባቢዉ ግጭት እንዲነሳና በዚያ ጥቅም በሌለዉ ግድብ ክዚህ በፊት በሺራሮና በባድመ ላይ እንደተደረገዉ ሁሉ የኢትዮጵያዉያንን ደም በማፍሰስና እነሱ እየዘረፉ ለመኖር የዘረጉት ወጥመድ ነው። ግድቡ ከፍ ብሎ ከተሰራ ወደ ሌሎች ኣካባቢዎች ወደ ምስራቅና ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ተዘርግቶ ሌሎች የሀገሪቱ ኣካሎች ይጠቀሙ ነበር ። ነገር ግን ያ ባለመፈለጉ የግድቡ ስራ ኤሌክትሪክ ለሱዳንና ለግብጽ ማመንጨትና መሽጥ ብቻ ሲሆን የተመረጠዉም ቦታ እድንበር ኣካባቢ ነው:: ይህም በመሆኑ ድንገት ግጭት ቢከሰት እድንበር ላይ በመሆኑ በግብጽም ሆነ በሱዳን በቀላሉ የሚመታና የሚመክን ነዉ። ልክ ወደ ትግሬ የባቡር ሃዲዱ ሲዘረጋ አማራዉንና ኦሮሞዉን አግልሎ ወይም ሳይነካ ከአዋሽ ተነስቶ ዳር ዳሩን እየዞረ በአፋር በረሀ እንደ ደጋን ጎብጦ ከተጉአዘ በሁዋላ ወደ ቀኝ በመታጠፍ የትግሬ ከተሞችን አዳርሶ እንደቆመው የባቡር መንገድ አይነት መሆኑ ነው።

ሐ) ሶስተኛዉ ትልቁ የሴራው አካል በአባይ ግድብ ስም እጂግ ግዙፍ የሆነ የኢትዮጵያ ሀዝብ ገንዘብ በህጋዊ መልክ መዝርፍና ማደህየት ነው። በዚህ ግዙፍ የዝርፊያ ስልት በኑሮ ውድነት ላይ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች አርሶ ኣደሮች ነጋዴዎችና ሌሎች የህበረተሰብ ክፍሎች ካፋቸዉ እየተነጠቁ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለማይጠቅምና በራሳቸዉ ላይ ችግር ለሚፈጥር ሰራ እየተበዘበዙ (እየገበሩ) ነው። በሌላ በኩል በጣም የሚያሳዝነዉ ወያኔዎች የዘርፉትና በግልጽ አለም ካወቀዉ ገንዘብ ዉስጥ 3 .00 ቢሊዮን በመለስ ሰም የተቀመጠ ሲሆን 11.70 ቢሊዮኑ ደግሞ ከኢትዮጵያ ውስጥ በህገወጥ መንገድ ተዘርፎ የሽሸ ነው። ይህ ማለት ወያኔወች የዘርፉት ገንዘብ ብዛት አራት የአባይ ግድቦችን ሊያሰራ የሚችል በመሆኑ ኢትዮጵያ በመድማት ላይ መሆኑዋን የዉጭ ሚዲያዎ በግልጽ ጽፈዋል።

መ) ሌላዉ ኣስገራሚ ሚስጥር አልጃዚራ ላይ ከግብጽ ከኢትዮጵያና ከእንግሊዝ አገር ተጋብዘው በተደርገው ዉይይት ላይ ግብጻዊቱዋ እዲህ ብላለች ” ግድቡ ሀገራዊ (ናሽናል) ሳይሆን ክፍለ አሁጉራዊ (ሪጂናል) መሆኑን ሙዋቹ መለስ ዜናዊ ተስማምቶበታል” በማለት የዎያኔዉ መሪ ክህደት መፈጸሙን አጋልጣለች (ይህንን ታሪካዊቪዲዮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማየት ኣለበት)። ይህም ማለት የግደቡ ባለቤቶች ሱዳን ግብጽና ሌሎች በአካባቢዉ የሚገኙ ሀገሮች ጭምር ናቸዉ ማለት ነው::

ከዚህም አልፎ ተርፎ ዜጎች መሰዋእትን ከፍለዉ ባቆዩዋት ሀገር ዉስጥ መብታቸዉን በመጠየቃቸዉ ብቻ በጸራራ ጸሃይና በድብቅ ሲገደሉ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ወገኖቻችንን ከሚኖሩበርት ቦታ በግፍ እያፈናቀሉ የነጻነት ታጋዮችን እያሳደዱ እየደበደቡ እያሰሩና እያሰቃዩ ለህዝቡ ጠላት ከመግዛት በስተቀር ለእድገት ለማይጠቅም ግድብና በአባይ ስም ለኢትዮጵያ አሳቢ መስሎ ለመታየት እየሞከሩ ነው። ፕሮጀክቱ ሲነደፍ በጥላቻና ግዙፍ ገንዘብ ለመዝረፊያ በመሆኑ በአጠቃላይ ኢትዮጵያዉያንንና በአባይ ተፋሰስ አካባቢ ኑዋሪ የሆነውን ሰፊ ሕዝብ አላማከሩም። ህዝቡም ሃሳቡን ተጠይቆ አልተሳተፈበትም።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወያኔ ለአንተ በታሪክ ዉሰጥ ጥሩ አስቦም ሆነ ሰርቶ ስለማያዉቅ በምትወደዉ ወንዝሕ በአባይ ሽፋን የተጋረጠብህን ተንኮል በጣጥሰህ ወያኔን በማስወገድ በሚጠቅምህ መልኩ አባይንና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችህን ወደፊት ለመገንባት ስለምትችል አሁን ወያኔ በሚነዛው የዉሸትና ፕሮፓጋንዳ እንዳትረታ።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

Teddy Mesganaw

posted by Tseday Getachew

ሐረርነት እና ጎንደርነት! በሰሎሞን ተሰማ ጂ.

አዳላህ እንዳልባል እንጂ፣ የዚህ መጣጥፍ ርዕስ “ጎንደርነት እና ሐረርነት”ም ቢባል አያወዛግብም፡፡ ነገር ግን፣ ሐረር ከጎንደር በምስረታዋም ሆነ በቀደምትነቷ የታወቀች ስለሆነ ነው ርዕሳችንን ሐረርነት እና ጎንደርነት ያልነው፡፡ እንደምታውቁት ስለሐረርነት እና ስለጎንደርነት ማውራት ማለት፣ ስለሐረሬዎች ወይም ስለሐረሪዎች ማውራት አይደለም፡፡ በተመሳሳይ መልኩም፣ ስለጎንደርነት ማውራት ማለት፣ ስለጎንደሬዎች ማውራት ማለት አይደለም፡፡ የዛሬዎቹ ሐረሬዎችም ሆኑ የዛሬዎቹ ጎንደሬዎች ከመፈጠራቸው ብዙ መቶ አመታት በፊትም ሐረርነት እና ጎንደርነት ነበሩ፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ልናወሳው የፈለግነው ስለሁለቱ ከተሞች ሳይሆን ስለታሪካቸው፣ ስለስነ-ሰብዓቸው፣ ስለሃይማኖታቸው፣ ስለፖለቲካቸው፣ ኤኮኖሚያቸውና ስለባሕላቸው ነው፡፡ በጥቅሉ ይህ፣ ጽሑፍ የሐረር እና የጎንደር (ወይም አዳላችሁ እንዳንባል የጎንደር እና የሐረር) ፖለቲካዊ ፍልስፍናን በደሕና መስኮት ወደውስጣቸው ለማሳየት የሚጥር ይሆናል፡፡ (በበሩ ገብቶ ሐረርነትን እና ጎንደርነትን በቅጡ ማወቅ የሚፈልግ ካለ፣ ጠቀም ያለ ገንዘብ ቆጥቦ/ቋጥሮ ለቀናት ወይም ለወራት ያህል ቢጎበኛቸውና ቢያጠናቸው ይበጃል፡፡) ሐረርነት እና ጎንደርነት ብዙ-ብዙ ምስጢራትን የተሸከሙ ጽንሰ-ሃሳቦች ናቸው፡፡

ሐረርነት እና ጎንደርነት!

http://ethioforum.org

posted by Tseday Getachew

ለሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

የትግራይ ህዝብ ነፃ ኣውጭ ድርጅት (ት. ህ. ነ .ኣ. ድ) በየካቲት ወር 1968 ዓ.ም ባወጣው የመጀመሪያ ዕትም መፅሔት ላይ ዐማራ የትግራይ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ነው በማለት የፖለቲካ አቋሙን ግልጽ አድርጓል። በዚህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ግለሰብ ደግሞ ዓለምሰገድ ዓባይ ይባላል፤በትግራይ ክልል ውስጥ ባደረገው ጥናት 82 በመቶ የሚሆኑ የትግራይ ተወላጆች ተጀምሮ እስኪያልቅ ዐማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው ማለትን በጥናቱ ማጠቃለያ ላይ አረጋግጧል። በትናንትናው ዕለት ትግራይ ኦንላይ የተሰኘው የትግሬዎች ድረገጽ በአሁኑ ሰዓት በአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ተገቢ ነው በማለት በጥላቻ የተሞላ ግልጽ አቋሙን አሳውቋል። ይህ ደግሞ በዐማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ብዙዎች እንደሚሉት በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ እንደሚፈጸመው ዓይነት አጠቃላይ የሰብዓዊ መብት ረገጣና የመልካም አስተዳደር እጦት አለመሆኑን በግልጽ ያሳያል። ጉዳዩ የመንግስትን ስልጣን በጨበጡ በወያኔ ትግሬዎች የሚፈጸም ሥር የሰደደ ጥላቻና በአንድ ዘር ላይ ያነጣጠር ጥቃት በመሆኑ ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ በረጋና በሰከነ መንፈስ ሊመለከተው ይገባል። ያማራ ድምፅ እንደ አንድ ሀላፊነት የሚሰማው ዜጋ ያለምን ማቅማማት በትግራይ ነፃ አውጭዎች እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በተጭባጭ ማስረጃ አስደግፎ ለኢትዮጵያ ለህዝብ ያሳውቃል። እርሶም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ የሚችሉትን በማድረግ በሀገራችን ላይ ያንዣበበውን ጥፋትና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ሊያመራ የሚችል አደጋ በመከላከል የዜግነት ግዴታችንን በጋር እንወጣ።

posted by Tseday Getachew

 

‹‹እኛ ንፁሆች ነን እየተወነጀልን ያለነው በተቀነባበረ ድራማ ነው›› አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ

 

-አቶ መላኩ ፈንታ ሆስፒታል ተኝተው እየታከሙ ነው

-ሁለት ተጠርጣሪዎች በዋስ ሲለቀቁ አንድ ተጠርጣሪ ተይዟል

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ኃላፊዎችና ነጋዴዎች ላይ 230 የሰው ምስክሮች መቆጠራቸው ታወቀ፡፡

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ሰኔ 17 እና 18 ቀን 2005 ዓ.ም. በእነ አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስና በእነ አቶ መላኩ ፈንታ የምርመራ መዝገብ ላይ ላለፉት 14 ቀናት የሠራቸውን የምርመራ ውጤቶች፣ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አቅርቦ አስረድቷል፡፡

መርማሪ ቡድኑ በእያንዳንዱ ተጠርጣሪ ላይ የሠራውንና የቀረውን የምርመራ ሒደት በዝርዝር ባያስረዳም፣ አልፎ አልፎ በአንዳንዳቹ ላይ የሰበሰበውን የሰነድ ማስረጃ ግልጽ ለማድረግ ከመሞከሩ ጐን ለጐን የምስክሮችን ቃል መቀበል በሚመለከት፣ የ96 ምስክሮችን ቃል መቀበሉን አስታውቋል፡፡ ቃላቸውን ያልተቀበላቸው 74 ምስክሮችና  60 የሙያ ምስክሮች እንደሚቀሩትም ተናግሯል፡፡

አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ አቶ በላቸው በየነ፣ አቶ ጥሩነህ በርታ፣ አቶ ተስፋዬ አበበ፣ አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር፣ አቶ ምሕረተአብ አብርሃ፣ አቶ ሙሌ ጋሻው፣ አቶ አሞኘ አወቀ፣ ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይና አቶ ተወልደ ብርሃን ገብረ መድኅን በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ለ14 ቀናተ ያከናወናቸውን የምርመራ ተግባራት መርማሪ ቡድኑ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡ ከቀረጥ ነፃ የገቡ የሆቴልና የግንባታ ዕቃዎች ለታለመላቸው ዓላማ አለመዋላቸውን የሚያስረዳ ሰነድ መሰብሰቡን፣ የተመሠረተን ክስ ከማቋረጥ ጋር በተያያዘ የሰነድ ማስረጃ መሰብሰቡንና የተወሰኑ የምስክሮች ቃል መቀበሉን ገልጿል፡፡ ሕገወጥ በሆነ የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ የገባ ሲሚንቶን አስመልክቶ ባለሥልጣኑ ክስ ቢመሠርትም ተጠርጣሪዎች በክሱ እንዳይካተቱ ማድረግን በሚመለከት፣ በአቶ ገብረዋህድ፣ በአቶ ነጋ፣ በአቶ አሞኘ አወቀና በአቶ ተወልደ ብርሃን ላይ ማስረጃ መሰብሰቡንና ቀሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች እንዳሉትም አስረድቷል፡፡

የተመሠረቱ ክሶች በሕገወጥ መንገድ እንዲቋረጡ ከተደረጉ 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ ቀደም ሲል ከሰበሰበው ማስረጃ በተጨማሪ ባለፉት 14 ቀናት 21 መዝገቦችን መሰብሰቡንና መመርመሩን፣ የምስክሮች ቃል መቀበሉን፣ በዚህ የወንጀል ተግባር የተጠረጠሩትም አቶ ገብረዋህድ፣ አቶ በላቸው፣ አቶ ተስፋዬና አቶ ሙሌ መሆናቸውን ለችሎቱ አስረድቷል፡፡

በመመሳጠርና በማስመሰል በሕገወጥ መንገድ የተወሰደ የጥቆማ አበልን በሚመለከት ሰነድ መሰብሰቡንና በዚህም የወንጀል ተግባር የተጠረጠሩት አቶ ገብረዋህድ፣ አቶ በላቸውና አቶ ጥሩነህ በርታ መሆናቸውን የገለጸው የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን፣ ከናዝሬት ወደ አዲስ አበባ የሚገባ ዕቃ ሳይፈተሽ እንዲያልፍ በማድረግ፣ ቃሊቲ ጉምሩክ ሲፈተሽ ሕገወጥ የታክስ ማጭበርበር ሥራ መሆኑ ተደርሶበት የተመሠረተን ክስ ያቋረጡና በድርጊቱ የተሳተፉት አቶ ገብረዋህድ፣ አቶ ነጋ፣ አቶ ምሕረተአብ፣ አቶ አሞኘና አቶ ተወልደ ብርሃን መሆናቸውን ጠቁሟል፡፡

በሕገወጥ መንገድ የኦዲት ሪፖርትን በመከለስና ገቢን በማሳነስ በናዝሬት፣ በሚሌና በድሬዳዋ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች ሳይፈተሹ በማሳለፍ በመንግሥትና በሕዝብ ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ወንጀል የተጠረጠሩት ደግሞ፣ ከአቶ ጥሩነህ በርታና ከኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይ በስተቀር ሁሉም መሆናቸውን የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ገልጿል፡፡ አቶ ገብረዋህድና አቶ ጥሩነህ በርታ የተጠረጠሩበት ሌላው ድርጊት ደግሞ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል የሚገቡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ክስ ተመሥርቶባቸው ፍርድ ቤት ከደረሱ በኋላ፣ ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉንና የኩባንያዎች የታክስ ኦዲት እንዲከለስ ማድረጋቸውን መርማሪ ቡድኑ አስረድተቷል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ለችሎቱ ማስረዳቱን ቀጥሎ እያለ፣ ፍርድ ቤቱ በመሀል ገብቶ ‹‹ተጠርጣሪ ኩባንያዎች ስንት ናቸው? ያጣራችሁትስ ምንድነው? ይኼንን ግልጽ አድርጋችሁ አስረዱ፤›› በማለት ጠይቋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ በርካታ ኩባንያዎች እንዳሉ በቃል ለመግለጽ ቢሞክርም፣ ለችሎቱ መግለጽ የቻለው የታዋቂው ነጋዴ አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር ንብረት የሆኑትን ነፃ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ፣ ባሰፋ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ፣ ሞኒት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ፣ አቶ ምሕረተአብ አብርሃ በባለቤትነት ይመሩታል የተባለው መፍአም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና አቶ አሞኘ አወቀ በባለቤትነት የሚመሩት እንግዳዬ አሰፋ ኮንስትራክሽን ማሽነሪ አከራይ ድርጅቶች መሆናቸውን ጠቁሟል፡፡

ጊዜ ቀጠሮ ባልተጠየቀባቸውና ለፍርድ ቤቱ ይፋ ባልደተረገበት ሁኔታ በኩባንያዎቹ ላይ የሚደረገው ምርመራ አግባብነትን በሚመለከት ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ቡድኑ ያነሳውን ጥያቄ፣ ሕገ መንግሥቱ በሚያዘው መሠረት በኩባንያዎቹ ባለቤቶች ላይ ምርመራ ሲደረግ በመካከላቸው ትስስር አለ ተብሎ ስለሚገመት መሆኑን መርማሪ ቡድኑ በመናገር ብዙም ግልጽ ሳይደረግ ታልፏል፡፡

ባለፉት ሦስት የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜያት በተደረጉት ምርመራዎች ሥልጣንን አላግባብ በመጠቀም ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተደረጉ 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ 45 መሰብሰቡንና ምርመራ ማድረጉን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ፣ ቀሪ 15 የተቋረጡ የክስ መዝገቦች እንደሚቀሩ፣ ከላይ እንደጠቀሰው 96 የሰዎች ምስክሮች ቃል ቢቀበልም 74 ምስክሮችና 60 የሙያ ምስክሮች እንደሚቀሩት፣ በተጠርጣሪዎች ላይ የሰነድ ማስረጃ ቢሰበስብም የሚቀረው እንዳለ፣ በክልል የባለሥልጣኑ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች የሚሰበሰቡ ሰነዶች እንዳሉትና ከኦዲት ምርመራ ጋር በተያያዘ የባለሙያ ማብራሪያ እንደሚቀረው አስረድቷል፡፡

የአቶ ገብረዋህድ ባለቤት ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይን በሚመለከት፣ በተጠርጣሪዋ የተሰወረ ሰነድ መኖሩን ፍንጭ በማግኘቱ ክትትል እያደረገ መሆኑን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ኮሎኔሏ የሞኒት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ተቀጣሪ ሆነው ሲሠሩ የባለቤታቸውን ሥልጣን ተጠቅመው በጥቅም በመተሳሰር ከግብር ስወራ ጋር መጠርጠራቸውንና ቀሪ ምርመራ እንደሚቀረው ለችሎቱ በማስረዳት፣ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎቹ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀድለት በወንጀል ሕግ ቁጥር 59(2) መሠረት ጠይቋል፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተፈቀደለት ጊዜ የሠራቸውን የምርመራ ክንውኖች አስረድቶ እንደጨረሰ በጠየቀው ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ላይ ተጠርጣሪዎች የሚሉት ካለ ፍርድ ቤቱ ጠይቋቸው፣ የአቶ ገብረዋህድ ጠበቃ በቅድሚያ አጭር መከራከሪያ ነጥብ አንስተዋል፡፡ ኮሚሽኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል በጀመረበት ጊዜ ማለትም ከ42 ቀናት በፊት በቂ ማስረጃ መሰብሰቡን መግለጹን ያስታወሱተ የአቶ ገብረዋህድ ጠበቃ፣ መርማሪ ቡድኑ ተጨማሪ ጊዜ እየጠየቀ ያለው በተሠራ ሥራ ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መጠየቁንም ተቃውመዋል፡፡

ተጨማሪ የሚያስረዱት ነገር እንዳላቸው የገለጹት አቶ ገብረዋህድ ሲፈቀድላቸው፣ ‹‹መርማሪ ቡድኑ ክስ መሥርቶ የጠረጠረበትን ወንጀል በማስረጃ አረጋግጦ ወንጀለኛነታችንን በፍርድ ቤት ሳያረጋግጥ፣ ጉቦ እየተቀበሉ በማለት ደምድሞ መናገሩ ሊታረም ይገባል፡፡ እኛ ንፁሆች ነን፡፡ ይኼ ከአለቆቻቸው ጋር ያቀነባበሩት ድራማ ነው፤›› ብለዋል፡፡ በዳኞች ፈቃድ የ14 ቀናት ጊዜ እየተፈቀደ ሁለተኛ ወራቸው መሆኑን ያከሉት አቶ ገብረዋህድ ‹‹ለዚች አገር የሠራን ዜጐች ነን፤ አገልግለናል፡፡ የእነሱን ድራማ ብቻ እየሰማን መቀጠል የለብንም፤›› በማለት ስሜታዊነት የተቀላቀለበት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የወንጀል ሕግ ቁጥር 59(2) በጠባቡ ካልተተረጐመ ማቆሚያ እንደሌለው በመግለጽ፣ መርማሪ ቡድኑ ባለፉት ቀጠሮዎች ከሠራው ውጭ ምንም የሠራው ነገር እንደሌለ ለችሎቱ በማስረዳት፣ የደንበኛቸው የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅላቸው የጠየቁት የአቶ በላቸው ጠበቃ ናቸው፡፡ ‹‹ከአንድ ወንጀል ወደ ሌላ ወንጀል እየተዘለለ ነው፡፡ እኔን በእስር ላይ በማቆየት የወንጀል መመሥረቻ ሰነድ እየተፈለገ ነው፡፡ ይኼ የሚያመለክተው ደግሞ በእኔ ላይ ምንም ዓይነት ወንጀል አለመገኘቱን ነው፡፡ ኮሚሽኑ፣ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እንዲሁም ፌዴራል ፖሊስ በጋራ በመሆን መላ አገርን የሚያዳርስ ኃይል ያላቸው ናቸው፡፡ በእኔ ላይ የቀረቡትን ሁለት ክሶች እንዴት ባለፉት 40 ቀናት አጣርተው ማቅረብ ያቅታቸዋል?›› በማለት የጠየቁት ደግሞ አቶ ጥሩነህ በርታ ሲሆኑ፣ በዋስ ቢወጡ ከላይ ከጠቀሱት ኃይሎች ሊሰወሩ የማይችሉ መሆኑን በመግለጽ፣ ባለቤታቸው ምንም ገቢ የሌላቸው መሆናቸውንና በሁለት ሕፃናት ልጆቻቸው ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ከግምት በማስገባት ዋስትና እንዲፈቀድላቸው በተደጋጋማ ጠይቀዋል፡፡

አቶ ተስፋዬ አበበም የተጠረጠሩበት ወንጀል ግራ እንዳጋባቸው ተናግረው፣ ቀደም ሲል ከአራጣ ጋር እንደተጠረጠሩ ሰምተው አሁን ደግሞ ከቀረጥ ነፃ ከገቡ የሆቴልና የግንባታ ዕቃዎች ጋር መጠርጠራቸው እንዳስገረማቸው ገልጸዋል፡፡ የልብና የኮሌስትሮል ሕመም እንዳለባቸው ደጋግመው በማስረዳት፣ ለአገራቸው ዲሞክራሲ ግንባታና ለልማት ያደረጉት አስተዋጽኦን ከግምት ውስጥ በማስገባት የዋስትና መብታቸውን እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡

ተጠርጥረው ሲያዙ የተነገራቸው ባልተፈቀደ የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ ሲሚንቶ በማስገባት መጠርጠራቸውን፣ ቀጥሎ ከናዝሬት ወደ አዲስ አበባ የሚገባ ዕቃ ሳይፈተሽ እንዲያልፍ በማድረግ መጠርጠራቸውንና እንዲሁም በኮንትሮባንድ ንግድ የተከሰሱን ተከሳሾች ክስ በማቋረጥ፣ ወዘተ በማለት ላለፉት 42 ቀናት በእስር ላይ መቆየታቸው አግባብ አለመሆኑን የገለጹት የአቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር ጠበቃ ናቸው፡፡ ‹‹መርምሬ አልጨረስኩም ማለት ተጠርጣሪዎችን የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብታቸውን መንፈግ ነው፤›› ያሉት የአቶ ነጋ ጠበቃ፣ ላለፉት 42 ቀናት በደንበኛቸው ላይ በዝርዝር የተሠራ የምርመራ ውጤት አለመቅረቡን፣ ምን ያህል ምስክር በእሳቸው ላይ ተቆጥሮ ምን ያህሉ እንደተሰማና እንዳልተሰማ በማብራራት ከዚህ በላይ ደንበኛቸው በእስር መቆየት እንደሌለባቸው ተናግረዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ የጠየቀው የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ውድቅ ተደርጐ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ውጪ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡

አቶ ምሕረተአብ አብርሃን በሚመለከት መርማሪ ቡድኑ ከባለሥልጣናቱ ጋር በመመሳጠር ክስ በማቋረጥ ተጠርጥረው እንደታሰሩ ቢያስረዳም፣ ጠበቃቸው ክሱ እንዳልተቋረጠና አሁንም በጠቅላይ ፍርድ ቤት እየታየ መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡ ቃላቸውን ሰጥተው በማጠናቀቃቸውም የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸው ከእስር እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡ የኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይ ጠበቃ በደንበኛቸው ላይ የተጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ተቃውመዋል፡፡ ኮሎኔል ሃይማኖት ‹‹የአቶ ነጋን ሰነድ ሊያሸሹ ይችላሉ፣ የተሸሸገ ሰነድ እንዳለ ፍንጭ አግኝተናል ግን አልያዝንም፤›› የሚባለው ነገር የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብታቸውን የሚገፉ መሆኑን በመግለጽ ተቃውመዋል፡፡ ሌላው ኮሎኔል ሃይማኖት ያነሱት ነጥብ ጡረተኛ መሆናቸውን ሲሆን፣ ጡረታቸውን ሄደው ለመቀበል ባለመቻላቸው በአጃቢ ሆነው መቀበል እንዲችሉ እንዲታዘዝላቸው በጠበቃቸው አማካይነት ጠይቀዋል፡፡

ኮሎኔል ሃይማኖት ተጨማሪ ሊያስረዱት የሚፈልጉት ጉዳይ እንዳላቸው በማመልከት ሲፈቀድላቸው ‹‹እናት ነኝ፤ ልጆቼ ተበትነዋል፡፡ እስቲ እናትና አባት ሆናችሁ፣ በሕግ ጥላ ሥር ሆናችሁ ልጆቻችሁ ሲበተኑ ምን ይሰማችኋል?›› በማለት ጥያቄያቸውን ለችሎቱ ዳኞች አቅርበው፣ ልጆቻቸው አጉል ዕድሜ ላይ በመሆናቸው ወደ ጐዳና ይወጣሉ የሚል ሥጋት እንዳደረባቸው ተናግረዋል፡፡ የወለደ አንጀት የሚሰማውን ሁሉም እንደሚያውቀው በማከል፣ አንደኛው ልጃቸው ጀማሪ ተማሪ በመሆኑ ተረጋግቶ ለማጥናት አለመቻሉን፣ ጠዋትና ማታ እነሱን ለማየት ወደ እስር ቤት እንደሚመላለሱና ‹‹አስቤዛ አልቆብናል›› የሚል ሪፖርት እንደሚልኩባቸው አስታውቀዋል፡፡ ‹‹እኔ ሕግ የሚለኝን ሁሉ ለመሆን ዝግጁ ነኝ፤ በምጠየቅበት ነገር ልጠየቅ፤ እነዚህ ልጆች ግን ምን ይሁኑ?›› በማለት በድጋሚ ጠይቀው ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ጠብቆላቸው ልጆቻቸውን እንዲንከባከቡ ጠይቀዋል፡፡ ሌሎቹም በአቶ ገብረዋህድ የምርመራ መዝገብ ያሉ ተጠርጣሪዎች የመርማሪ ቡድኑን የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በመቃወም የዋስትና መብትቸው እንዲጠበቅላቸው ጠይቀዋል፡፡

ሌላው ሰኔ 18 ቀን 2005 ዓ.ም. የታየው የምርመራ መዝገብ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎችን ያካተተው የእነ አቶ መላኩ መዝገብ ነበር፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በእነ አቶ ገብረዋህድ የምርመራ መዝገብ የሠራውን የምርመራ ክንውን በተመሳሳይ በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብም ማከናወኑን ገልጿል፡፡ በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብ ለየት ያለ መረጃ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው መርማሪ ቡድኑ፣ 1.3 ሚሊዮን ብር በቤታቸው ውስጥ ቀብረው እጅ ከፍንጅ የተያዙትን የተጠርጣሪ መርክነህ ዓለማየሁ ወንድምን አቶ ብርሃኑ ዓለማየሁንና የእነሱ ዘመድ መሆናቸውን የተናገሩትን አቶ ገተሮ ሐጢያን በዋስ መልቀቁን ማሳወቁ ነው፡፡

ለሆቴል ቤት ዕቃና ለግንባታ በሚል ከቀረጥ ነፃ ገብተው ለሌላ ዓላማ ስለዋሉ ዕቃዎች፣ ስለ ግብር ስወራ፣ ታክስ ማጭበርበር፣ ክስ ማቋረጥ፣ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ሳይፈተሹ ስለማሳለፍ፣ ምንጩ ያልታወቀና ተገቢ ያልሆነ ሀብት ማፍራትና ሌሎችንም በተጠርጣሪዎቹ ተፈጽመዋል ባላቸው የወንጀል ድርጊቶች ዙሪያም ምርመራ አድርጐ ሰነድ መሰብሰቡንና የምስክሮች ቃል መቀበሉን መርማሪ ቡድኑ አብራርቷል፡፡ የሚቀሩት ሥራዎች እንዳሉም በመግለጽ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ጠይቋል፡፡

አንድ ተጠርጣሪ ለምርመራ ተጠርቶ ቃሉን ከሰጠ በኋላ በማረፊያ ቤት የሚቆይበት የሕግ አግባብ እንደሌለ በመግለጽ፣ ደንበኛቸው በማረፊያ ቤት ከ47 ቀናት በላይ መቆየታቸው ከሕግ አግባብ ውጭ በመሆኑ የመርማሪ ቡድኑ ጥያቄ ውድቅ ተደርጐ ደንበኛቸው እንዲሰናበቱ የጠየቁት የአቶ መላኩ ፈንታ ጠበቆች ናቸው፡፡ አቶ መላኩ ቃላቸውን ሰጥተው ስለጨረሱ በዋስ ሊለቀቁ ወይም የሕግ አማካሪዎቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ማግኘት የሚችሉበት ማረሚያ ቤት እንዲዛወሩ ጠይቀዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ በቀረበ ቁጥር ጊዜ ቀጠሮ እየጠየቀ ያለው ፍርድ ቤቱ ጠበቅ ያለ ትዕዛዝ ስለማይሰጥ መሆኑን የገለጹት ጠበቆቹ፣ አቶ መላኩ ከተያዙ ጀምሮ ጠበቆቻቸውንም ሆነ ቤተሰቦቻቸውን በሕገ መንግሥታዊ መብታቸው መሠረት አግኝተው እንደማያውቁ ተናግረዋል፡፡ ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውም እየተጣሰ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ምርመራው ቢቀጥል ተቃውሞ እንደሌላቸው ጠበቆቹ ለችሎቱ አስረድተው፣ አቶ መላኩ ግን በዋስ እንዲለቀቁ ወይም ሰው ወደሚያገኙበት ማረሚያ ቤት እንዲዛወሩ በድጋሚ ጠይቀዋል፡፡

ዶ/ር ፍቅሩ ተፈራ የተጠረጠሩት፣ ‹‹ለእነ አቶ መላኩ ፈንታ ጉቦ ሰጥተሃል›› በሚል መሆኑን የገለጹት ጠበቃቸው፣ ሰኔ 14 ቀን 2005 ዓ.ም. መርማሪ ጠርቷቸው፣ ‹‹ከእነ አቶ መላኩ ጋር ያለህ ነገር ተዘግቷል አንፈልግህም፤›› እንዳሏቸውም አክለዋል፡፡ በመሆኑም ዶ/ር ፍቅሩ የሚያጠፉት ሰነድና የሚያባብሉት ምስክር ስለሌለ ምርመራቸው ያለቀው ከአንድ ወር በፊት በመሆኑ በዋስ እንዲለቀቁ አመልክተዋል፡፡ ሌሎቹም ተጠርጣሪዎች የመርማሪ ቡድኑን ተጨማሪ የ14 ቀናት ጊዜ ተቃውመው፣ እንዲሁም በየጊዜው ምርመራው እየሰፋ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ እልባት ሊሰጠው እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ደንበኞቻቸው በዋስ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡

መርማሪ ቡድኑ በሰጠው መልስ፣ አቶ ገብረዋህድ፣ ‹‹የኮሚሽኑ ሥራ ድራማ ነው›› ማለታቸው ትክክል ባለመሆኑ ፍርድ ቤቱ ተግሳጽ ጭምር እንዲሰጥላቸው፣ አቶ መላኩም ከጠበቃና ከቤተሰቦቻቸው እየተገናኙ በመሆኑ አቤቱታው ውድቅ እንዲደረግላቸው፣ አቶ መላኩ ፖሊስ ሆስፒታል በሪፈራል ተኝተው እየታከሙ መሆናቸውንና ፍርድ ቤትም የቀረቡት ከሆስፒታል መሆኑን፣ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ዙሪያ የሚሰበሰብ ቀሪ ሰነድ እንዳለ፣ የምስክሮችንና የባለሙያዎችን ቃል መቀበል እንደሚቀረው አስረድቷል፡፡ የተጠርጣሪዎቹ ጥያቄ ውድቅ ተደርጐ ለቀሪ ምርመራው የጠየቀው የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀድለት በድጋሚ አመልክቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ በሁለቱም የምርመራ መዝገቦች በሰጠው ትዕዛዝ፣ ኮሎኔል ሃይማኖት ከአጃቢ ጋር ሆነው ጡረታቸውን እንዲቀበሉ አዟል፡፡ መርማሪ ቡድኑ በቀጣይ ቀጠሮ በእያንዳንዱ ተጠርጣሪ ላይ ስንት ምስክር እንደሰማ፣ ስንት እንደቀረውና ሌላም የሠራው ነገር ካለ በተናጠል እንዲያቀርብ አዟል፡፡ መርማሪ ቡድኑ የሠራውን የምርመራ ሥራ ተመልክቶ ብዙ የምርመራ ሥራ ማከናወኑን መገንዘቡን ገልጾ፣ የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ መፍቀዱንና የተጠርጣሪዎች የዋስትና መብትን አለመቀበሉን አስታውቋል፡፡ አቶ መላኩ ፈንታ ቤተሰብና የሕግ አማካሪ አይጠይቃቸውም ለተባለው ጥያቄም ሰብዓዊ መብት ይከበር ብሏል፡፡ መርማሪ ቡድኑ ባሹ ዘርጋው የሚባል የባለሥልጣኑ የቃሊቲ ጉምሩክ ዋጋ ተማኝ ኦፊሰርን በቁጥጥር ሥር አውሎ የ14 ቀናት ጊዜ ጠይቆበታል፡፡

ethiopian reporter

posted by Tseday Getachew

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን”

“ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”

tesfaye1

 
“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡– ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- መታሰርህን ለቤተሰብ ተናግረሀል?
ወጣት ተስፋዬ:- ለማንም ሰው እንድናገር አልፈቀዱልኝም፤ መስሪያ ቤቴ አልጠየቀኝም፣ ደሃዋ እናቴ ያለችው ናዝሬት ነው እሷም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ አባቴ አቶ ተካልኝ አስተማሪ ነበር አርባ ጉጉ ላይ ነው በ1985 ዓ.ም በነበረው ግጭት ነው የተገደለው፡፡ ማንም ሳይጠይቀኝ፣ፍ/ቤት ሳልቀርብ 23 ወር ታሰርኩ ልብስ ምግብም የሚያመጣልኝ ሰው አልነበረም፡፡ እናቴም መታሰሬን እንኳ አታውቅም መስሪያ ቤቴም ስኮላርሽፕ አግኝቷል፤ ወደ ውጪ ሃገር ሊማር ሊሄድ ነው የሚባል ነገር ስለነበረ አልጠየቁኝም፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የት ነበር ስኮላርሺፕ ያገኘኸው?
ወጣት ተስፋዬ:- የዛሬ 2 ዓመት አካባቢ የራስመስ ሙንደስን ስኮላርሽፕ አግኝቼ ነበር፡፡ ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ካሊፎርኒያና ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ቶክዮ ባሉ ምሁራን ሪኮመንድ ተደርጌ በጣሊያኑ ፌራሪ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ እንደተፈታሁ ሄጄ ስጠይቃቸው ብዙዎቹ ጓደኞቼ በጣም ደነገጡ፡፡ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ቅማል ተወርሬ … ባካችሁ ተውኝ … ምንም የሌለ ነገር የለም በጣም ተጎድቻለሁ፡፡ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ እናቴ ጋ ስሄድ በጣም ደነገጠች፣ በሕይወት ያለሁ አልመሰላትም 23 ወር ሙሉ ከቤተሰብ ስለተለየሁ ግራተጋባች፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በእስር ወቅት የደረሰብህ ድብደባና ማሰቃየት ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ በኤሌክትሪክ ጀርባዬ ላይ አቃጥለውኛል፣ በብልቴ ላይና በኩላሊቴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ስላደረሱብኝ ሽንት ችዬ አልሸናም፣ ሽንቴን መቆጣጠርም አልችልም፡፡ ኩላሊቴንም በጣም ያመኛል፡፡ ውሃ ውስጥ እየነከሩ በጣም ደብድበውኛል፡፡ አሁን ስናገር ያመኛል ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እንደው ስታስበው ለእስር ያበቃህ ወይም ከመንግስት ጋር ያጋጨህ አጋጣሚ ነበር?
ወጣት ተስፋዬ:- መስሪያ ቤቴ ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ነበሩ፤ በጣም ይከታተሉኛል፡፡ በቢ.ፒ.አር ላይ ስብሰባ በተደጋጋሚ ይጠራ ነበር፡፡ እኔም ሠራተኛ ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ነገሮች ሲመጡ እኔ አልቀበልም በግልፅ እናገር ነበር፤ ሠራተኛውም እኔን ይደግፋል፡፡ ከመታሰሬ ጥቂት ጊዜ በፊት ገነት ሆቴል ስብሰባ ነበረን፡፡ በዛ ስብሰባ ላይ በጣም ተከራከርኩ፤ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አቶ ፀጋዬ ማሞ የሚባሉ አሰልጣኝ፣ ከውጭ ጉዳይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና ከንግድና ኢንዱስትሪም የመጡ ነበሩ ስማቸውን የማላስታውሳቸው ባለስልጣን ነበሩ፤ እዛ ላይ ሀሳብ አንስቼ ተከራክሬ ነበር፡፡ “የሠራተኛን ሀሳብ ዳይቨርት ያደርጋል” ይሉኝ ነበር፡፡ መቼም ግን ሀሳቤን በመናገሬ ይህን የመሰለ ስቃይ ይደርስብኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ “አሸባሪ፣ ግንቦት ሰባት” እያሉ እኔ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ፍርድ ቤት ሳልቀርብ ያለምንም ፍርድ በርሜል ውስጥ ውሃ ጨምረው እያስተኙ አሰቃዩኝ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እንደዚህ ያሰቃዩህ ምን አይነት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ ነው?
ወጣት ተስፋዬ:- እኔን ጥፋተኛ የሚያስደርግ ምንም መረጃ አላገኙም፣ እኔን አስረው ወደ መስሪያ ቤት በተደጋጋሚ ይደውሉ እንደነበር ይነግሩኝ ነበር፡፡ የኢሜይል አድሬሴንም ተቀብለው በርብረዋል ግን ምንም አላገኙም፡፡ እኔ ከማንም ጋር ሊንክ የለኝም ኢሜሌ ላይ የስኮላርሺፕ መልዕክት ካልሆነ በስተቀር ምንም የለውም፡፡ በመስሪያ ቤቴ ሪሰርቸር ነበርኩ፣ በሶሲዮሎጂ ነው የተመረኩት፡፡ ሉሲ የተገኘችበት ሣይት ላይ አፋር፣ ጋምቤላ ብዙ ሳይቶች ሰርቻለሁ፡፡ ከአለቆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሰላማዊ ነው እነሱ ናቸው ስኮላርሽፕ ሪኮመንድ ያደረጉኝ፡፡ አንደኛው ፕሮፌሰር 25 ዓመት ሙሉ እዚህ አገር ሰርቷል፣ አርዲን ያገኘው እሱ ነው፡፡ ሄነሪ ጊልበርት ይባላል፤ እሱም ሪኮመንድ አድርጎኛል፡፡ እኔ በጣም የሚቆጨኝ ደሃዋ እናቴ አረቄና ጠላ ሸጣ ነው ያስተማረችኝ ምን ብዬ ልንገራት እንደዚህ አትጠብቀኝም ከበደኝ፣ አሁን እሷ የምትሰጠኝ ምግብ ራሱ ደምደም አለኝ… (ረጅም ለቅሶ)፡፡ ልጄ በደህናው አይደለም የጠፋው ሞቷል ወይም መኪና ገጭቶታል ብላ ነበር የምታስበው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የከመታሰርህ በፊት ፖለቲካ ተሳትፎ ነበረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- 1997 ዓ.ም የቅንጅት ደጋፊ ነበርኩ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ በ97 የነበረው ሁኔታ ስንት ሰው አለቀ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነበር ታውቃላችሁ ምንም የምናደርገው ነገር አልነበረም ፡፡ በምርጫ አሸንፎ ሥልጣን መያዝ እንደማይቻል ተረዳሁኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም በኋላ የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አልሆንኩም፡፡ ከዚህ በኋላ ከምንም ነገር የተገለልኩ ሆኛለሁ፡፡ አንድ ብርጭቆ ሳትሰብር አሸባሪ ስትባል አስብ እንግዲህ አንድ ብርጭቆ እንኳን ሰብሬ አላውቅም ባለኝ እውቀት እንደውም ለእውቀት ነው የምጓጓው እውቀቴን አሳድጌ አገሬን ለመለወጥ ነው የማስበው እኔን ምንም የሚመለከተኝ ነገር የለም አሸባሪም ግንቦት ሰባትም አይደለሁም፡፡ስትደበደብ፣ ስትሰቃይ ያላደረከውን አድርጌያለሁ ትላለህ፤ በርሜል ውሃ ሞልተው ይከቱሃል ያሰቃዩሃል፡፡ አያሳዝንም ይሄ? እንዴት አድርጎ እዚህ አገር ይኖራል? 23 ወር ሙሉ አስረው ማሰቃየታቸው ሳያንስ የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል፡፡ እኔ ግን ከዚህ በላይ ሞት የለም ብዬ ነው የነገርኳችሁ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- አሁን የት ነው የምትኖረው?
ወጣት ተስፋዬ:- መኖሪያ የለኝም … (ረጅም ለቅሶ)

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝን ለመርዳት የምትፈልጉ አንባብያን ከፍኖተ ነፃነት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (ምንጭ ፍኖተ ነጻነት)

http://www.goolgule.com

posted by Tseday Getachew

በአቃቤ ሕግና በፍረድ ቤቱ መካከል አለመስማማት እየነገሰ መሆኑ ተሰማ!

ቅዳሜ ሰኔ 15/2005

‹‹ዳኞቹ እናንተ ናችሁ እኛ?›› ከዳኞቹ መካከል አንዱ ለአቃቤ ሕጎቹ ከተናገረው!

የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የክስ ሂደትን ታክኮ በአቃቤ ሕግና በዳኞች መካከል አለመስማማት መፈጠሩ ተነገረ፡፡ አለመስማማቱ የተፈጠረው አቃቤ ሕግ ለተደጋጋሚ ጊዜ በችሎት ውስጥ ከዳኞች ጭምር የበላይ መሆኑን ለማሳየት ጥረት በማድረጉ ነው ተብሏል፡፡ በዚሁ እያገባደድነው ባለው ሳምንት ተሰይሞ ምንም ሳያከናውን ተበትኖ በነበረው ችሎት ላይ አቃቤ ሕግ ቀድሞ ለፍርድ ቤት ሪጂስትራ ገቢ ማድረግ የነበረበትን ሲዲ እዚያው ለችሎቱ ገቢ ለማድረግ መሞከሩና ሲዲውን ገቢ ማድረግ የነበረበት ክሱ በተመሰረተበት ወቅት ማለትም (ከስድስት ወራት በፊት) ሆኖ ሳለ እስከአሁን ሳያስገባ መቆየቱ በዳኞቹና አቃቤ ሕጎቹ መካከል ፍጥጫ ጭምር እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፡፡Ethiopian Musilms

ባለፉት ስድስት ወራት በነበሩት የችሎት ትእይንቶች በዳኞችና በአቃቤ ሕጎች ግንኙነት እንዲሁም የዳኞችን ሚና በመጫወት ላይ የሚገኙት አቃቤ ሕጎች መሆናቸውንና ይህም ምንም አይነት ፍትሀዊ አያያዝም ሆነ ፍርድ ከፍረድ ቤቱ ልንጠብቅ እንደማንችል በምንሰራቸው የችሎት ዘገባዎች ስንገልጽ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም ይህ የአቃቤያን ሕጎች ከማንም በላይ ሆኖ በችሎት ለመታየት የሚያደርጉት ጥረት ዳኞችን ብስጭት ውስጥ ከትቶ ጠንካራ ቃላት እንዲሰነዝሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ እንደ ፍረድ ቤት ምንጮች ዘገባ በእለቱ ችሎት መጀመር የነበረበት ከማለዳ 2፡30 ቢሆንም ዳኞች ፍረድ ቤት የደረሱት ከረፋዱ 4 ሰዐት ነበር ሆኖም አቃቤ ሕጎች ከዳኞች ጭምር በአንድ ሰዓት በመዘግየት ከቀኑ አምስት ሰአት መድረሳቸው የውዝግብ መነሻ ሊሆን ችሏል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግም አንዱ ዳኛ ‹‹ዳኞቹ እናንተ ናችሁ እኛ?›› የሚል ንግግር የሰነዘሩ ሲሆን አቃቤ ሕግ የበላይ ሆኖ ለመታየት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያቆምም ጠይቀዋል፡፡

ይህ አጋጣሚ በችሎቱ ውስጥ እንዲሁም በአጠቃላይ በፍትህ ስርአቱ ውስጥ ያለውን የአድልኦ አሰራር አመላካች የነበረ ሲሆን መንግስትም ንጹሀን ሰዎች ላይ የፈጠራ ወንጀሎችን በመደርደር ለማስወንጀልና ለማስፈረድ የማይቸገር መሆኑን አመላካች ነው፡፡ የአቃቤ ሕጎቹ በቂ ማስረጃ ሳይዙ በልበ ሙሉነት በፍርድ ቤቱ የበላይ ሆኖ ለመታየት የሚያሳዩት እብሪትም ከዚህ የመነጨ መሆኑን መታዘብ ይቻላል፡፡ ያለ አሳማኝ ምክንያት ችሎቱን በዝግ (ማንም እንዳይገባ በማድረግ) ማስኬድ፣ ለፍረድ ቤቱ ገቢ ሊሆኑ የሚገባቸውን ሰነዶች ገቢ አለማድረግ፣ የፍረድ ሂደቱን ማጓተት፣ ተከሳሾችን ማሳቀቅ፣ ከዳኞች የበላይ ሆኖ መታየት፣ ችሎት ላይ አርፍዶ መድረስ፣ የጠየቀውን ሁሉ ዳኞች እንዲቀበሉት ማድረግ እና የመሳሰሉት ከአቃቤ ሕግ በኩል ሲታዩ የነበሩ የፍትህ ስርአቱን አንካሳነት በጉልህ አመላካች የነበሩ ሂደቶች ናቸው፡፡

አላሁ አክበር!

http://ecadforum.com/Amharic/archives/8618/

posted by Tseday Getachew

 
 

Post Navigation