Fitih le Ethiopia

I wish democracy and unity for Ethiopia

Archive for the month “September, 2014”

የታገደው ድፍረት ፊልም የይገባኛል ጥያቄ አስነሳ

አንጀሊና ጆሊ ኤግዚኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰር የሆነችበትና ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ዲፕሎማቶችና የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በብሔራዊ ቴአትር ሊመረቅ የነበረው ድፍረት ፊልም፣ በፍርድ ቤት እግድ ከተቋረጠ በኋላ የይገባኛል ጥያቄ ማስነሳቱ ታወቀ፡፡

ፊልሙ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ የሚያጠነጥነው አስገድዶ የደፈራትን የ29 ዓመት ወጣት በገደለችው የ14 ዓመት ታዳጊ አበራሽ በቀለ (በፊልሙ ሒሩት) ሕይወት ዙሪያ ነው፡፡ ደፋሪዋ ሕፃኗን በጠለፋ ሊያገባትም ሙከራ አድርጐ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር መሥራች የሆኑት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ጉዳዩን ሰምተው ጥብቅና ቆመውላት ራስን ለመከላከል በሚል በነፃ እስከተለቀቀችበት ጊዜ ድረስ፣ አበራሽ በግድያ ክስ ተመሥርቶባት ማረሚያ ቤት ነበረች፡፡

በአቶ ዘረሠናይ ብርሃኔ መሐሪ የተጻፈውና ዳይሬክት የተደረገው ይህ ፊልም በዚህ ዓመት በሰንዳንስ ፊልም ፌስቲቫል ተሸላሚ መሆኑን ተከትሎ፣ የታሪኩ ባለቤት በሆነችውና ፈቃደኝነቷን እንዳልተጠየቀች በምትናገረው ወ/ሪት አበራሽና የወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ወንድምና የታሪኩ ጸሐፊ ነኝ በሚሉት አቶ ፍቅሩ አሸናፊ ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡

የፍርድ ቤት እግዱ እንደሚያሳየው በከሳሽነት የቀረቡት አቶ ፍቅሩ አሸናፊና ወ/ሪት አበራሽ በቀለ ሲሆኑ፣ ተከሳሾቹ ደግሞ አቶ ዘረሠናይ ብርሃኔ፣ ኃይሌ አዲስ ሥዕሎች ድርጅትና ትሩዝ ኤይድ ሚዲያ ድርጅት ናቸው፡፡

ክሱ እንደሚያስረዳው ድፍረት የተሰኘው ፊልም ተመርቆ ለሕዝብ ዕይታ ቢውል በከሳሾች ሞራላዊና ኢኮኖሚያዊ መብት ላይ የማይተካ ጉዳት ሊደርስ እንደሚችል በመገንዘብ፣ ፍርድ ቤቱ ፊልሙ ለሕዝብ ዕይታ እንዳይውል ወይም እንዳይመረቅ ጭምር እገዳ ጥሏል፡፡ በተጨማሪም በተከሳሾች ላይ ሊደርስ ለሚችል ኪሳራ ከሳሾች 50 ሺሕ ብር በዋስትና አስይዘዋል፡፡

ወ/ት አበራሽ እንደምትለው ፊልሙ በርሊን እስከተመረቀበት ጊዜ ድረስ ምንም ዓይነት መረጃ አልነበራትም፡፡ ከሰባት ወራት በፊት ግን አቶ ዘረሠናይን አግኝታው በፊልሙ ላይ ዕውቅና እንዲሰጣት፣ የተወሰነ ገንዘብም እንዲከፍላት እንደምትፈልግ ገልጻለት የነበረ ቢሆንም ይህ ሳይሆን ቀርቷል፡፡

የፊልሙ ሥራ የእሷን ደኅንነት ከግንዛቤ ውስጥ ያስገባ አይደለም በማለት የምትወቅሰው ወ/ት አበራሽ፣ ምንም እንኳ ሁኔታውን ለማስረዳት ብትሞክርም ከአቶ ዘረሠናይ በመጨረሻ ያገኘችው መልስ አዎንታዊ አለመሆኑን ትናገራለች፡፡ ‹‹ከተፈጠረው ነገር ጋር በተያያዘ የምኖረው ተደብቄ ነበር፡፡ ይኼ ፊልም ግን ታሪኩን እንደ አዲስ ቀስቅሶ የእኔንም የቤተሰቦቼንም ሕይወት አደጋ ላይ ጥሎታል፤›› ትላለች፡፡

ወ/ት አበራሽ የደፈራትን ሰው ከገደለች በኋላ በኦሮሞ የእርቅ ባህል ጉማ መሠረት ቤተሰቦቿ ካሳ ከፍለው ነገሩ ተቋጭቶ ነበር፡፡ በስምምነቱ መሠረት እሷም ቀዬዋን ጥላ ለመውጣት ተስማምታ እንደነበር የምትናገረው አበራሽ፣ ‹‹በባህሉ መሠረት ሴት ገድላ ካሳ መክፈል አትችልም፡፡ ስለዚህም ወደ አካባቢዬ እንዳልመለስ የሟች ቤተሰቦች ያስጠነቀቁኝን በመስማትና ለቤተሰቦቼ ደኅንነት ስል ለዓመታት እዚያ ሳልደርስ ቀረሁ፤›› ብላለች፡፡

በአሁኑ ወቅት ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችን ለማገዝ የሚሠራ ሀረም በተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ በመሥራት ላይ የምትገኘው ወ/ት አበራሽ፣ በሕይወቷ ብዙ ውጣ ውረዶችን እንዳሳለፈች ትናገራለች፡፡ የትውልድ ቦታዋ ቀርሳ አርሲን የለቀቀችው ወ/ት አበራሽ ሁለተኛ ደረጃ እስክትደርስ የኖረችው ቀጨኔ ሕፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ነበር፡፡ ታሪኳ ተካትቶ በተሠራ ዘጋቢ ፊልም አማካይነት ታገኝ የነበረው ገንዘብ ኮሌጅ ስትገባ መቋረጡን ታስታውሳለች፡፡ ስለዚህም በነበረባት የገንዘብ ችግር የኮሌጅ ትምህርቷን ለማቋረጥ መገደዷን፣ ከዚያም ወደ ዱባይ እስከሄደችበት ጊዜ ድረስ በአንድ ትንሽ የፊልም ሲዲ ማከራያ ሱቅ ውስጥ መሥራቷን ለሪፖርተር ገልጻለች፡፡

አቶ ዘረሠናይ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ላይ እንደተናገረውና አቶ ፍቅሩ እንደሚሉት ስለታሪኩ መጀመሪያ አቶ ዘረሠናይ የነገረው ለእርሳቸው ነው፡፡ ይህ የሆነው እ.ኤ.አ. በ2005 ሲሆን፣ አቶ ፍቅሩ እንደሚሉት የፊልሙ ሐሳብ የተወሰደው ከእሳቸው በመሆኑ ፊልሙን በጋራ ለመሥራት አስበው ነበር፡፡ ‹‹ከ2008 በኋላ አቶ ዘረሠናይ እኔን ለማናገር አልፈለገም፡፡ እንዲያውም ይደበቀኝ ጀመር፤›› ይላሉ፡፡

የፊልሙን መሠራት ሲጠባበቁና ነገሮችን ሲከታተሉ እንደነበር፣ የአበራሽን ይሁንታም እንዳገኙ አቶ ፍቅሩ ይናገራሉ፡፡ አቶ ዘረሠናይ ግን ለእሷም ለእሱም የታሪኩ ሐሳብ ባለቤት እንደመሆኑ ዕውቅና ሳይሰጥ መቅረቱን ያስረዳሉ፡፡ ‹‹ያለሷ ታሪክ ፊልሙ አይሠራም ነበር፡፡ ባትደፈር፣ በጥንካሬ ደፋሪዋን ባትገድለው ኖሮ ታሪክ አይኖርም ነበር፤›› ይላሉ አቶ ፍቅሩ፡፡

በፊልሙ ውስጥ ሌላ ባለታሪክ የሆኑትና በወቅቱ የ14 ዓመቷ ታዳጊ ጠበቃ የነበሩት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ለፊልሙ ዳይሬክተር ታሪካቸው በፊልሙ እንዲካተት ፈቃድ መስጠታቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ይህንንም ያደረጉት ታሪኩ በፊልም መሠራቱ የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ጥያቄን ያራምዳል፣ ስለጠለፋና ስለጥቃት ግንዛቤ ለመፍጠር ያስችላል በሚል እንጂ ‹‹የእኔ ታሪክ ይነገር›› በሚል እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

ለአበራሽ ጥብቅና በቆሙላት ጊዜ ከዚያም በኋላ አበራሽ በመኖሪያ ቤታቸው ተቀምጣ እንደነበር ቅርበትም እንደነበራቸው የሚያስታውሱት ወ/ሮ መዓዛ፣ ለረዥም ዓመታት ግን ከአበራሽ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ሳይኖራቸው እንደቆዩም ይናገራሉ፡፡

ከፊልሙ መሠራት በኋላ ግን የታሪካቸው በፊልም መሠራት ለአበራሽ የሚከፍተው የዕድል በር ይኖራል በሚል ማፈላለግ መጀመራቸው የሚናገሩት ወ/ሮ መዓዛ፣ ስለጉዳዩ በነገሯት መሠረት በመጨረሻ የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ ደራርቱ ቱሉ የአበራሽን ስልክ ቁጥር እንደሰጠቻቸውና እንዳገኙዋት ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

‹‹ደውዬ ወደ አዲስ አበባ አስመጣኋት፡፡ አሁንም ያለችው እናቴ ቤት ነው፡፡ የእኔ ቤት ወጣ ስለሚል ነው እዚያ እንድትቀመጥ ያደረግኩት፡፡ ከመጣች ወደ ሰባት ወራት ገደማ ሆኗል፤›› የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፣ ወ/ት አበራሽን አሁን እየሠራችበት ያለው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት እንድትቀጠር ያደረጉት እሳቸው እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡

ወ/ሮ መዓዛ እንደገለጹት ወ/ት አበራሽ ወደ አዲስ አበባ እንድትመጣ ያደረጉት ፊልሙ ጀርመን በርሊን ውስጥ ሊመረቅ በተቃረበበት ጊዜ ነበር፡፡

ለታሪኳ ባለቤት ወ/ት አበራሽ በፊልሙ ሥራ ተሳታፊ ከሆኑት ግለሰቦች ሁሉ ቅርበት ያላት እርሷ እንደመሆኗ የታሪኳ ባለቤት ተጠቃሚነትን በሚመለከት ለወ/ሮ መዓዛ ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹መጠቀም እንዳለባት አምናለሁ፡፡ አቶ ዘረሠናይም በዚህ ያምናል፡፡ ይህን ለማድረግም በጣም ፈቃደኛ ነው፡፡ እሷም የምትጠብቀው ነገር አለ፡፡ ችግር የፈጠረው እንዴት በሚለው ላይ አለመነጋገር ነው፤›› ብለዋል፡፡

ወንድማቸው አቶ ፍቅሩ አሸናፊም ፊልሙ ላይ ጥያቄ ማንሳታቸውን በሚመለከት፣ ወንድማቸውና የድፍረት ፊልም ዳይሬክተርና ከፕሮዲዩሰሮቹ መካከል አንዱ የሆነው አቶ ዘረሠናይ ምንም እንኳ የጓደኝነታቸውን ደረጃ መናገር ባይችሉም፣ ጓደኛማቾች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ወንድማቸው ስለ እርሳቸው ለጓደኛው አቶ ዘረሠናይ ሲያወሩ የፊልም ባለሙያ የሆነው አቶ ዘረሠናይም ታሪኩን ወደ ፊልም ለመቀየር ትልቅ ፍላጐት እንዳደረበትና የፊልሙ መነሻ እንዲህ እንደነበር፣ ከዚህ ውጪ ግን በወንድማቸውና በአቶ ዘረሠናይ መካከል ሌላ ጉዳይ ይኑር አይኑር የሚያውቁት እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ግጭቱ ቀላል እንደሆነ ስለዚህም በጣት በሚቆጠሩ ቀናት ውስጥ ይፈታል የሚል እምነት እንዳላቸው አክለዋል፡፡

የፊልሙ ዳይሬክተር አቶ ዘረሠናይ ብርሃኔ በእጁ ላይ ያለው የፍርድ ቤት እግድ ብቻ በመሆኑ ስለክሱ ዝርዝር ነገር ሳያውቅ በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት አስተያየት መስጠት እንደማይፈልግ ለሪፖርተር አስታውቋል፡፡ የባለታሪኳ ወ/ሮ አበራሽ ፈቃድን ማግኘት አለማግኘቱን በተመለከተም አቶ ዘረሠናይ ምንም ማለት አለመፈለጉን ገልጿል፡፡ ጠበቃው ዓርብ ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ የክሱን ቻርጅ ለማግኘት ፍርድ ቤት እንደነበሩና የክሱን ዝርዝር እንዳወቁ ለቀረቡለት ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጥ ገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ዓርብ እኩለ ሌሊት ድረስ ከእሱ በኩል የተሰማ ነገር አልነበረም፡፡

የፊልሙ እግድ ለብሔራዊ ቴአትር ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. አሥራ አንድ ሰዓት ላይ መድረሱን ከሳሾች ቢጠቁሙም፣ የቴአትር ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሽመልስ እግዱ የደረሰው አሥራ አንድ ሰዓት ከሃያ አምስት ላይ እንደነበር ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

እሳቸው እንዳሉት እግዱ በደረሰበት ወቅት 1,200 ያህል እንግዶች አዳራሹ ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አሥር ያህሉ አምባሳደሮችና ባለሥልጣናት ነበሩ፡፡ በአሳጋጆቹ በኩል የነበረው አቀራረብ አስቸጋሪ ስለነበርና በሌላኛውም በኩል ፊልሙን ለማቋረጥ ያለመፈለግ ነገር ስለነበር፣ በአጋጣሚው የአገር ገጽታ እንዳይበላሽ በጥንቃቄ ለመያዝ ቴአትር ቤቱ የተለያዩ ጥረቶችን አድርጓል ብለዋል፡፡

‹‹የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይከበራል፡፡ ይህ ምንም ዓይነት ጥያቄ የለውም፡፡ ነገር ግን በሁሉቱም በኩል የነበረው ነገር ወደ ግጭት የሚያመራ ዓይነት ስለነበር ነገሩ በሰላም እንዲፈታ ፖሊስ ጠርተናል፡፡ ምክንያቱም እኛ ያለን የፀጥታ ኃይል ያን ማድረግ አይችልም ነበር፤›› ሲሉ አቶ ተስፋዬ የነበረውን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡

posted by Tseday  Getachew

http://satenaw.com

“በሽብር” ተከሶ ፍ/ቤት የቀረበው ወጣቱ ፖለቲከኛና መምህር አብርሃ ደስታ የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀበት

ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ ዛሬ በግምት 9፡00 ሰዓት ፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ ሲደርስ በግቢው የነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባሎች እንዲሁም የአብርሃ ደስታ ደጋፊዎች በጭብጨባ ያላቸውን አክብሮት የገለጹለት ሲሆን እሱም አጸፋውን መልሷል፡፡ ከማዕከላዊ አጅበውት የመጡት የፌዴራል ፖሊሶች ለምን አጨበጨባችሁ እያንዳንዳችሁ ትገባላችሁ በማለት እያስፈራሩ ግቢውን ለቃችሁ ውጡ በማለት ከግቢ ለማስወጣት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ጉዳዩን ሊከታተል የመጣው ታዳሚም ለምን እንወጣለን አንወጣም እኛም ችሎት ተገኝተን ልንከታተል ሲገባ ግቢ ውስጥ መቆምም ልትከለክሉን ነው በማለት ተቃውሞ በማሰማቱ ችሎቱ እስኪጠናቀቅ በግቢው እንድንቆይ ተደረገ፡፡ የክሱ ጉዳይ የታየው በችሎት ሳይሆን በጽ/ቤት ነበር፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታም ከጠበቃዬ ጋር ልገናኝ አልቻልኩም፣ ዘመድ አዝማድም ሊጠይቀኝ አልቻለም በማለት ለፍ/ቤቱ አስረድቷል፡፡

ዳኛውም ከጠበቃና ከቤተሰብ ጋር የማታገናኙ ከሆነ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ፖሊስ ተጨማሪ ማስረጃና ምስክር ለማሰባሰብ የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቁ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮውን ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ተቃውመውታል ፖሊስ ደንበኛዬን ከመያዙ በፊት ማስረጃና ምስክሮችን ማዘጋጀት ነበረበት ነገር ግን አሁንም ደንበኛዬ ታስረው ማስረጃና ምስክር ሊባል አይገባም፣ እስራቱ ህገወጥ ነው በማለታቸው ዳኛው እንዳትሰራ አደርግሃለሁ ጥብቅናህን በፍትህ ሚ/ር አሳግድብሃለሁ በማለት እንዳስፈራሯቸው ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም ዳኛው ፖሊስ የጠየቀውን የጊዜ ቀጠሮው ፈቅደው ለመስከረም 22ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 እንድትገኙ በማለት ችሎቱ ተጠናቋል፡፡ አብርሃ ከችሎቱ ሲወጣም የሱን ጉዳይ ሊከታተል የመጣው ታዳሚ በጭብጨ ሸኝቶታል፡፡

posted by Tseday Getachew

http://satenaw.com

 

ሐሰን ሺፋ ከፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነርነት ሥልጣናቸው ተነሱ

ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት ነባር ታጋዮች መካከል አንዱ የነበሩትና ሕወሓት በተከፋፈለበት ወቅት የነስዬ አብርሃ ወገንን ተቀላቅለው በኋላም ወደ አቶ መለስ ወገን ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱት የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሐሰን ሺፋ ከስልጣናቸው እንዲነሱ መደረጉ አነጋጋሪ መሆኑን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመለከቱ።
hasen shifa
የፌዴራል ፖሊስ የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች እንደገለጹት አቶ ሐሰን ሽፋ በተለይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ እንቅስቃሴን የሕወሓት መንግስት እንዳሰበው በተንኮል ሊቆጣጠረው ካለመቻሉና በስርዓቱ ባለስልጣናት ውስጥ በተነሳው ያለመተማመን ችግር ጋር ተያይዞ ካሉበት ቦታ እንዲነሱ ተደርገዋል። አቶ ሐሰን በምክትል ኮምሽነርነት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሩን ከታች ሆነው ሲዘውሩ የቆዩ ሲሆን በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በጋምቤላ፣ በትግራይ፣ በአማራ ክልል፣ በደቡብና በሌሎችም ስፍራዎች ሥርዓቱ ለፈጸማቸው ጭፍጨፋዎች ተጠያቄ እንደሆኑ የሚናገሩት የዘ-ሐበሻ ምንጮች በድንገት ከዚህ ስልጣናቸው ተነስተው ወደ ፌደራል ጉዳዮች ሚ/ር መስሪያ ቤት ውስጥ እንዲሰሩ መላካቸው የስርዓቱን ደጋፊዎች ሳይቀር “ድርጅቱ በውስጡ ምን እየሆነ ነው?” በሚል እያነጋገረ ነው ብለዋል።

በሕወሓት/ኢሕአዴግ አገዛዝ ስር ያሉ ባለስልጣናት እርስበእርሳቸው አለመሰማማታቸው እንዲህ ያሉ ከስልጣን መነሳቶችና/ መዘዋወሮች በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።

posted by Tseday Getachew

“ጉድ በል ጎጃም አለ ያገሬ ሰው!” የወያኔኢሕአዴግ ተላላኪው የዳላሱ ወጣት ኢብራሂም ሲራጅ ማን ነው?

በሚሊዮን ኢትዮጵያ(ከዳላስ)https://i0.wp.com/www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2014/09/dallas1.png

dallas1ወያኔ/ኢሕአዴግ በውጭ ሃገር የሚኖሩት ኢትዮጵያውያንን ለማደራጀት የሚያስችላቸውን የጥፋት ውጥን በመወጠን ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍል ተወልደውያደጉ ለሆዳቸው ያደሩ አደርባዮችን በመመልመል የቤት ስራውን እየሰራ ይገኛል። አያሌ ኢትዮጵያውያን የስርአቱን አስከፊነት በመገንዘብ ሳይወዱ በግድ የሚወዱት ሃደራቸውና ሕዝባቸውን ትተው ቢሰደዱም እንኳን እስካሉበት የስደት ሃገር በመከተል የከፋፍለህ ግዛ መሰሪ ፖሊሲያቸውን ለማስፈጸም በፖሊሲ ደረጃ በመንደፍ የጥፋት ተግባራቸውን ገፍተውበታል። በዚህም መሰረት ምንም እንኳን እዚህ ገቡ የሚባሉ ቁጥር ያላቸው አባላት ማፍራት ባይችሉም ጥቂት ርካሽ ተውዳጅነት ለማትረፍና የግል ንዋይ ፈላጎታቸውን ለማሟላት ከመራሹ መንግስት ጋር በመተባበር ህዝብን ለማወናበድና ለማታለል የሚተጉ ግን አልጠፉም። ኢብራሂም ሲራጅ ከእነዚህ በጥቅም ከተደለሉትና የመሰሪው የወያኔ መንግስት ተልእኮ ለመወጣት ሌት ተቀን ደፋ ቀና ከሚሉት አንዱ ነው።

ዳላስ በወያኔ መሰሪ ተባባሪዎች እጅ ወድቃለች ማለት ባይቻልም እነዚህ ጥቂት ርዝራዦት በኮሚኒቲ፣ በቤተክረስቲያንና በሌሎችም ኢትይጵያዊ በሆኑት ተቓማት እጃቸውን በማስገባት ቀላል የማይባል የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመወጣት ሌት ተቀን ደፋ ቀና እያሉ ለቱባ የወያኔ አለቆቻቸው ታማኝ ለመሆን ተግተው ይሰራሉ። ምንም እንኳን በኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች አላማቸውን ማሳካት ባይችሉም። የጥፋቱ ሰለባ ከሆኑት ኢትዮጵያዊ ተቓማት ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያንና (http://www.stmichaeleoc.org/) በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር (http://maaecdallas.org/) ዋና ተጠቃሽ ናቸው። በእነ አቶ ተፈራወርቅ (ጋሻው ኢንሹራንስ) የሚመራው የጥፋት ቡድን አማካኝነት ቤተክርቲያኒቷን ፍርድ ቤት ሶስት ጊዜ በመክሰስ በሺዎች የሚቆጠሩ ዶላሮች ወጪ ዳርገዋል። ኮሚኒቲውም ምርጫ በመጣ ቁጥር የወያኔ ጀሌዎቻቸውን ለማስረጽ ህዝብን በማወናበድ ላይ ይገኛሉ። ከወራት በኳላ የሚደረገውን የመራዳጃው ማህበር የቦርድ አባላት ምርጫ ላይ የወያኔ አባላትን ለማስገባት ተጽዕኖ ለመፍጠር የቤት ስራቸውን እየሰሩ ናቸው። ይህ እውነታ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ሁሉም የኮሚኒቲው አባላት ኮሚኒቲው በወያኔ እጅ እንዳይወድቅ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሊታደገው ይገባል።

እነዚህ የጥፋት ሃይሎች እራሳቸውን “ሰበቡ” የሚል ስያሜ በመስጠት በእነ ተኮላ፣ ደምመላሽ፣ ተፈራወርቅና ሌሎችም መሪ ተዋናይነት የሚመራ ሲሆን ሁሌም ምክንያት እየፈጠሩ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጉሮሮ በተነጠቀ በወያኔ በተመደበላቸው ባጀት ስጋዊ ፍላጎታቸውን የሚያስደስቱ ለሌላው ግድ የሌላቸው ህሊናቸው የሸጡ አገርና ሕዝብን የካዱ የግል ጥቅማቸውን ብቻ የሚያዩ ስንስቦች ናቸው። የማህበሩ አባላት ለሚሰሩት የጥፋት ተልዕኮ ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ በትውልድ ቀዬያቸው በህገ ወጥ መንገድ ከድሃው ምስኪን የሃገሬ ገበሬ መሬት እየተነጠቀ ለውለታቸው የመኖሪያና የንግድ ቦታ መስሪያ ይሰጣቸዋል። ኢብራሂም ሲራጅ የዚህ ማህበር ተላላኪ እንደመሆኑ መጠን የጽዋው ተቓዳሽ በመሆን በባህር ዳር ከተማ ሲኒማ ቤት መስሪያ ቦታ ለውለታው ተችሮታል። እነዚህ የጥፋት ሃይሎች ኢትዮጵያውያን በሚሳተፉበትና የገቢ ማሰባሰቢያ ቦታዎችን በመገኘት ወያኔኢሕአዴግ ለዚህ ተግባር በተመደበውብ ባጀት በመለገስ ሕዝብን ለማወናበድና የኮሚኒቲው ተቆርቓሪ ለመምሰል ይጥራሉ።

የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ፕላን(GTP) በተመለከተ የወያኔ/ኢሕአዴግ ቱባ ባለስልጣናት ወደ ሰሜን አሜሪካ በመጡበት ወቅት ምንም እንኳን ጥሪው ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚመለከት ቢሆንም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለመታደም ግን አልታደሉም። ስብሰባው ለመታደም የተዘጋጀበት ስፍራ ብሄድም ውይይቱን ለመካፈል ከተነፈጉት አንዱ ነኝ። የኢትዮጵያ ጉዳይ የሁሉም እንጂ የወያኔ አባላት ብቻ አለመሆኑን እይርታወቅ ስብሰባውን ለጥቂት አባሎቻቸው ብቻ በደብዳቤ በመጥራት ሐገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ደብዳቤ የላች ሁም በማለት ወደ ስብሰባ አዳራሹ እንዳይገቡ ተደርገው በፖሊስ እንዲባረሩ ተደርገዋል። በዚህ ወቅት እንዳይገቡ የተደረጉ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ሲያሰሙ ለወያኔ የደህንነት አባላት የሚላክ ቪዲዮ በመቅረጽና ተቃውሞ እያሰሙ በነበሩት በመሳለቅ ኢብራኢም ሲራጅ ለወያኔ ታማኝነቱን አሳይቷል። ይህ ደግሞ ከሃገርና ህዝብ ክህደት በተጨማሪ ለዲያፖራው ማህበራሰብ ያለው ንቀት ምን ያህል እንደ ሆነ ያሳያል።

ኢብራሂም ሲራጅ በሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽን(ESFNA) ዳላስን ወክለው ከሚጫወቱት ሁለት የስፖርት ክለቦች አንዱ በሆነው ኢትዮ ዳላስ ውስጥ እስከ ዛሬ ድረስ ላለፉት 11 አመታት ስጫወት ነበር ብሎ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሰጠው ቃለ መጠየቅ በፍጹም ከውነት የራቀ መሆኑን ቡድኑ ውስጥ ከሚጫወቱት አባላት ለመረዳት ችያለሁ። ለነገሩ መች ኢቲቪ እውነት አውርቶ ያውቅና። ወያኔ ማለት የውሸት ከረጢት መሆኑን ከታወቀ ውሎ ሰንብቷል። ነገር ግን ቡድኑ አባላት ውስጥ በተፈጠረው አለመግባባት እጁን በማስገባት ከጀርባ በመሆን ለሁለት እንዲከፈሉና ልዩነታቸው በሰላም እንዳይፈቱ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል። ወጣቶቹ ችግራቸውን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ከዋናው ቡድን እራሳቸውን ላገለሉት አባላት የቅርብ ጓደኞቹና ዘመዶቹ በመመልመል የጥፋት ሴራውን ሲሸርብ ነበር። ምንም እንኳን ያሰበው አላማ ባይሳካለትም የመጨረሻ ግቡ ግን ወጣቶቹን በጥቅም በመደለል የዛሬ ሁለት አመት ገደማ በአብነት ገመስቀል መሪ ተዋናይነትና በሼክ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲን ሙሉ የገንዘብ ድጋፍ ለተቓቓመው የስፖርት ማህበር ለማስረከብ ነበር።

ኢብራሂም ሲራጅ በአሁን ሰአት ኢትዮጵያ የሚገኝ ሲሆን በኢትዮጵያ ቴሌቪሽን በእንግዳ ፓሮግራም በተደረገለት ቃለመጠየቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይካድ ለውጥ አለ፣ በውጭ ኃገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስለ ልማቱ የሚናገሩትን አልሰማም፣ ወያኔኢሕአዴግ በሚያደርጋቸው ሁሉም ስብሰባዎች መሪ ተዋናይ ነኝ፣ የፖንድ ሽያጭና በቅርብ የማውቃቸው አቅም ያላቸው ኌደኞቼን በማስተባበር ላይ ግንባር ቀደም ነኝ ይለናል። በዚህም አንባገኑ የወያኔ ስርአትን ቀንደኛ ደጋፊ መሆኑና መራሹ ወያኔ ልማታዊነት ምስክርነት ይሰጣል። ውሸታሙን ኢቲቪንና ወያኔን እውነትነት አስረግጦ በመናገር የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ውሸታም መሆኑን ይነግረናል። ይህ ደግሞ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያለው ንቀት ያሳያል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንባገነኑ ስርአት ለእስራት፣ ለስደት፣ ለሞት፣ ለረሃብ፣ ለእንግልትና ለስቃይ እየተዳረገ ባለበት ሁኔታ ወያኔን ማሞካሸትና ልማታዊነት መመስከር የህሊና ዳኝነት የጎደለው ከመሆን ውጪ ምን ይሉታል። ለመሆኑ ወያኔ የሚለውን የሚያስተጋባለትን እንጂ መች ሕሊና ያለው ሰው ይፈልግና።

ጀግናው በላይ ዘለቀ ያፈለቀችው ጎጃም ኢብራሂም ሲራጅ አሳድጋለች የናት ሆድ ዥንጉርጉር ይሉታል ይህ ነው። አንዱ የባህርዳር አንድ ክለብ የሚያሰነጥለው አብሮ አደጉ ስለ ኢብራሂም ሲራጅ ሲናገር ይህ ትልቅ ሃብታችን ነው ልንጠቀምበት ይገባል ብሎናል። ጀግናው በላይ ዘለቀ በተወለደበት ሃገር ሃገሩን ሽጦ ለሆዱ ያደረውን እንደ ሃብት ሲቆጠር ጉድ በል ጎጃም ማለት ይሄኔ ነው።

ውድ የሐገሬ ልጆች ሆይ ኢትዮጵያ ሃገራችን አንድነቷና ዳርድንበሯ ጠብቃ ልትቆይ የቻለችው ብዙ የደም መስዋዕትነት ተከፍሎባት እንድሆነ ሁሉም ጠንቀቆ የሚያውቀው ስለሆነ እኔ ልነግራች ሁ አልሻም ለቀባሪ ማርዳት እንዳይሆንብኝ። ዛሬ ግን ወያኔና ግብራበሮቹ ይህን ታሪክ ለማጥፋት የዘር ፖለቲካ በመከተል ህዝቡን አንድነቱን እንዳይጠብቅ በማድረግ፣ የገዛ መሬታችን ለጎረቤት ሀገራት አሳለፎ በመስጠት፣ ምስኪን ገበሬ በማፈናቀል ለውጭ ባለሃብት በመሽጥና ሌሎችም አያሌ መሰሪ ተግባራቸውን ገፍተውበታል። ወያኔ/ኢሕአዴግ ያለ ሕዝብ መልካም ፍቃድ ስልጣን በአፈሙዝ በማስፈራራት ቢቆናጠጥም ሕዝብ ያለመረጠው መንድስት ዘላቂነት ሊኖረው ስለማይችል ሰርጎገብ ከሆኑት የወያኔ ተላላኪዎች ሰላባ እንዳንሆን ነቅተን በመጠበቅ ማጋለጥ ይኖርብናል። የዚህ ጽሁፍም ዋናው አላማም ይህ ነው።

ኢብራሂም ሲራጅ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የእንግዳ ፕሮግራም ያደረገው ቃለመጠይቅ እዚህ በመጫን ይመልከቱ! http://www.diretube.com/engeda/ebrahim-serag

አንድ ሕዝብ!!!

አንድ ኢትዮጵያ!!!

ኢትዮጵያ ለዘላለም አንድነቷን ጠብቃ ትኑር!!!
http://www.zehabesha.com

posted by Tseday Getachew

በተማሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገለጸ

በትምህርት በኢህአዴግ ጽ/ቤትና በትምህርት ሚኒስትር ትብብር ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚሰጠው ስልጠና በተማሪዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተገልጾአል፡፡ በስልጠናው ሰነድ ላይም ተካትቷል፡፡ ‹‹የትምህርት ተቋማትን ወደ ትክክለኛው የትግል ስልት የመመለስ አስፈላነት›› በሚል አብይ ጉዳይ ላይ በተሳሳተ ስልት ይንቀሳቀሱ እንደነበር በመጥቀስ ‹‹ተማሪው ጥያቄውን የሚያቀርበው ትምህርቱን እየተማረ፣ የትምህርት ቤቱን ህግና ደንቦች እያከበረ ሊሆን ይገባል፡፡…..ህገ ወጥ ሆኖ ህጋዊ ምላሽ ማግኘት አይቻልም፡፡›› በሚል ‹‹ህገ ወጥ ከሆኑ›› ህገ ወጥ ምልሽ እንደሚጠብቃቸው ያስጠነቅቃል፡፡
UNiversity students

 

 

 

 

 

 

 

ሰንዱ አክሎም ‹‹በተማሪው ማህበረሰብ ውስጥ አፍራሽ አዝማሚያ ያላቸው ተማሪዎች ነውጥን ለማስፋፋት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በጥብቅ በመታልና የንብረት ውድመት እንዳይደርስ በጥብቅ መታል ይገባል፡፡ በቅድሚያ ራስን መነጠል እና ቀጥሎም የነውጥ ኃይል አራማጅና ደጋፊ የሆኑትን ማጋለጥና ትግል ማድረግ ይገባል›› በሚል በተማሪዎቹ ላይ ሊወሰድ የሚችለውን እርምጃ ይዘረዝራል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

posted by Tseday Getachew

http://www.zehabesha.com

 

Post Navigation